የ100 ሺሕ ሰዎች ጥሪ፡ ለኒያ ኦቲዝም ማዕከል ግንባታ የሚሆን ታሪካዊ ንቅናቄ !

Date:



በግንባታ ላይ የሚገኘውን የኒያ ኦቲዝም ማዕከል መጠለያ ሕንጻ ለአገልግሎት ለማብቃት 100 ሺሕ ሰዎች እያንዳንዳቸው 300 ብር በማዋጣት የሚሳተፉበት ታላቅ የንቅናቄ ጥሪ ቀረበ።

ከሚያዝያ 6 እስከ ግንቦት 1 ቀን 2018 ዓ.ም. የሚቆየው ይህ ዘመቻ፣ መዋቅራዊ ግንባታው ተጠናቅቆ በፊኒሺንግ ስራ ላይ የሚገኘውን ሕንጻ በፍጥነት ለማጠናቀቅ ያለመ ነው።

የማዕከሉ ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ እሌኒ ዳምጠው እንደገለጹት፣ ይህ ፕሮጀክት መሳካቱ ለማዕከሉ መስራችና ለዘርፉ ባለውለታ ለነበረችው ለሟቿ ዘሚ የኑስ ትልቅ መታሰቢያ የሚሆን ነው።

ይህ የገቢ ማሰባሰቢያ ንቅናቄ በኢትዮጵያ ለ24ኛ ጊዜ የሚከበረውን የኦቲዝም ቀን በማሰብ የተዘጋጀ ሲሆን፣ ህብረተሰቡ በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ ተላልፏል።

ማንኛውም በጎ አድራጊ ግለሰብ 9616 አጭር የጽሑፍ መልዕክት ቁጥርን በመጠቀም የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ የሚችል ሲሆን፤ የ100 ሺሕ ሰዎች መረባረብ የኦቲዝም ሕጻናትን ተጠቃሚ የሚያደርገውን ይህን ግዙፍ ሕንጻ ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ ወሳኝ ሚና ይጫወታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...