ቻይና የሱማሊላንድን መገንጠል አልደግፍም ስትል አስታወቀች

Date:

ቻይና ሱማሊላንድ እና ታይዋን እያደረጉት ያሉትን ግንኙነት በፅኑ ተችታለች።

ከቅርብ ግዜያት ወዲህ ተገንጣይ አገራቱ ትብብራቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ በተለያየ መንገድ ሲገልፁ ነበር።

ይሁንና በሱማሊያ የቻይና አምባሳደር የሆኑት ዋንግ ዩ ፤ ግንኙነታቸውን ተገንጣይነትን ለማስተዋወቅ የተጠነሰሰ ብለውታል።

‹‹በአለም ላይ ያለው አንድ ቻይና ነው፡፡ ታይዋንም የቻይና አንድ አካል ናት፡፡ በርካታ አገራት የቻይናን አንድነት ይደግፋሉ›› ያሉት አምባሳደሩ መሠረታዊው እውነትም ይሄ ነው ብለዋል።

አክለውም የሱማሊያን ሉአላዊ አንድነት ለማስጠበቅ የቤጂንግ መንግስት ከሱማሊያ ፌዴራል መንግስት ጋር በቅርበት እየሰራ እንደሚገኝ ነው የገለፁት ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከምዝገባ ካርድ ባሻገር፦ ለነገው ድምፅ የዛሬው ጥንቃቄ

ግዮን መጽሔት :- የምርጫ ካርድዎን በእጅዎ ይዘዋል? እንኳን ደስ...

በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ...

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...