አንጋፋው የሥነጽሑፍ ባለሞያ አስፋው ዳምጤ የሚመሰገንበት “ኑ ታላቅ እናክብር” የተሰኘ ዝግጅት ነገ መጋቢት 10 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 7:30 ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ቤት ይካሄዳል።
በዝግጅቱ ላይ አንጋፋ ደራሲያን፣ ሠዓሊያን፣የጥበብ ሰዎች ይገኙበታል ተብሏል።
የደራሲ አስፋው ዳምጤን 90ኛ ዓመት የልደት በዓል ለማክበር በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር በተሰናዳው በዚህ ዝግጅት ላይ ልዩና በውድ ዋጋ የታተመ መጽሔት ለጥቂት ሰዎች ብቻ እንደሚታደልም ተነግሯል።
