ኖ ሞር’ ቴአትር በአሜሪካ ለታዳሚ ሊቀርብ ነው

Date:

በአገር ውስጥ መድረኮች በነበረው ቆይታ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈው ‘ኖ ሞር’ (No More) የተሰኘው ቴአትር፣ የባህር ማዶ ጉዞውን በመጀመር በአሜሪካ ዴንቨር ኮሎራዶ ለታዳሚ ሊቀርብ ነው።

ተውኔቱ “በደል የፈፀሙ ሰዎች ተገቢውን ምላሽ ሊያገኙ ይገባል” የሚል ጠንካራ ማህበራዊ መልዕክትን በአስቂኝ ዘውግ አዋህዶ የያዘ ስራ ነው።

ቴአትሩ በኢትዮጵያ ለእይታ በበቃበት ወቅት አራት ተዋንያንን እና ሦስት የቴክኒክ ባለሙያዎችን በማሳተፍ ጥራት ያለው ዝግጅት ማቅረቡ ይታወሳል።

ለኮሎራዶው ዝግጅት በተደረገው ማሻሻያ መሰረት ቴአትሩ የመጀመሪያ ተዋንያን ላይ መጠነኛ ለውጥ ተደርጓል።

‘ኖ ሞር’ በሰው ልጅ ግንኙነት ውስጥ የሚፈጠሩ በደሎችንና ለበደሎቹ የሚሰጡ ምላሾችን በትውፊትና በዘመናዊ የቴአትር አቀራረብ የሚተነትን ነው።

ስራው በዴንቨርና አካባቢው ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የጥበብ ጥምን ለማርካት ታስቦ የተዘጋጀ ሲሆን፥ በቅርቡም የመድረክ ቀኑና የትኬት ሽያጭ ዝርዝር ይፋ እንደሚደረግ ተገልጿል።

ይህ ዝግጅት የኢትዮጵያ ቴአትር ከሀገር ውስጥ አልፎ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያለውን ተቀባይነት ለማሳደግ ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሎ ይታመናል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአዲስ አበባ ጉዳይ በሌሎች አጀንዳዎች ላይ የሚካሄደውን ምክክር ጥላ አጥሎበታል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በ25ኛ ቀን ውሎው በሥራ ቡድን ደረጃ...

አሁን ያለው ሙስና ካለፉት አምስት ዓመታት በእጅጉ ይበልጣል

የሥነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ያስጠናው ጥናት ላይ...

ትራምፕ በኢኮኖሚ ጫና ላይ ማተኮራቸውን ገለጹ

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዋሽንግተን ኢራንን ወደ ስምምነት ለማምጣት...

በችኮላና በጥድፊያ” የሚዘጋጁ ህጎች፣ በህግ አወጣጥ ስርዓቱ ላይ አለመረጋጋት እየፈጠሩ ነዉ

በኢትዮጵያ የህግ አወጣጥ ሂደት ውስጥ ተደጋጋሚ ማሻሻያዎች፣ የአዋጅ መሻሮችና...