አለርት ሆስፒታል የሕፃናት ዓይን ህክምና ማዕከል ሥራ ጀመረ

Date:

አለርት ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህፃናት ዓይን ህክምና ማዕከል ስራ አስጀምሯል። ማዕከሉ በህፃናት ላይ የሚደርስ ዓይነ ስውርነትን በመከላከል ረገድ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው ተብሎለታል።

በማዕከሉ የምርቃት መርሃግብር ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፤ በሕፃናት ላይ የሚደርስ ዓይነ ስውርነትና የዓይን ጤና ህመም ከህፃናቱ ባለፈ ወላጅ ላይ፣ ማኅበረሰቡ እና ሀገር ላይ ተፅዕኖ የሚያሳድር መሆኑን አንስተዋል።

ማዕከሉም የተሞላ የዓይን ህክምና በመስጠት የመማር፣ ማንበብ፣ መጫወት በአጠቃላይ ለህፃናቱ ከእይታ ባለፈ የወደፊት ተስፋ የሚሰጥ መሆኑን ገልፀዋል።

40 በመቶ የሚሆነው የሀገሪቱ የህዝብ ቁጥር ህፃናት መሆናቸውን ገልፀው፤ ዛሬ ላይ በህፃናት ላይ የሚሰራ ስራ ለነገ ሀገር እድገትና ብልፅግና የማይተካ ሚና ያለው መሆኑን አስታውቀዋል።

ማዕከሉም በህፃናት ላይ የሚደርስ የዓይነ ስውርነትና የዓይን ህመምን በመከላከል ረገድ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው ብለዋል።

የአለርት ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ ዶክተር ሽመልስ ገዛህኝ በበኩላቸው፤ ሆስፒታሉ የተሟላ ግብአትና ብቁ ባለሙያዋችን በመጠቀም ጥራቱን የጠበቀ የህፃናት የዓይን ህክምና በመስጠት በህፃናት ላይ የሚደርስ የዓይን ጤና እክልንና ብርሀንን በመመለስ የወደፊት ተስፋ የሚሰጥ መሆኑን ገልፀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...