አሜሪካ በኢትዮጵያ በ10 ቢሊዮን ዶላር ለሚገነባው የአፍሪካ ትልቁ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባቷ ተሰምቷል።
ይህም የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአፍሪካ ቀንድ የመጀመሪያው ትልቅ የቢዝነስ ተነሳሽነት ተደርጎ ተወስዷል።
የአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ አማካሪ ማሳድ ቡሎስ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ቀደም ብሎ በኢትዮጵያ ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት ሀገሪቱ ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኝነቷን አስታውቀዋል።
እንደ ቢዝነስ ኢንሳይደር አፍሪካ ዘገባ፣ ቡሎስ የአሜሪካ ዓለም አቀፍ ልማት ፋይናንስ ኮርፖሬሽን በፕሮጀክቱ እንደሚሳተፍ እና ከቦይንግ ጋር በመተባበር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ እና በአፍሪካ ባሉ ሌሎች ሥራዎች ላይ እየሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል።
