የቤንዚን፣ የነጭ ናፍጣ፣ የኬሮሲን፣ የቀላል ጥቁር ናፍጣ እና የከባድ ጥቁር ናፍጣ መሸጫ ዋጋ በመስከረም ወር ሲሸጥበት በነበረው እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ያስቀመጠው የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ ዋጋ ከመስከረም 21 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት 12:00 ሰዓት ጀምሮ ተፈጻሚ እንዲሆን አዟል።
የአውሮፕላን ነዳጅ የችርቻሮ መሽጫ ዋጋ በአዲስ አበባ ከተማ 120.10 ብር/በሊትር እንዲሆን በመንግሥት መወሰኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።
የነዳጅ ማደያዎች እና ኩባንያዎችም በነዳጅ ምርቶች ግብይት አዋጁና በአሠራር መመሪያው መሠረት ውሳኔውን ተግባራዊ እንዲያደርጉ መስሪያ ቤቱ አሳስቧል።
