- ከሚዘጉት ኤምባሲዎች 6ቱ በአፍሪካ የሚገኙ ናቸው ተብሏል
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት በኤርትራና ደቡብ ሱዳን የሚገኙትን ጨምሮ 10 ኤምባሲዎቹን ለመዝጋት ማቀዱ ተገለጸ።
ከኤምባሲዎቹ በተጨማሪ 17 ቆንስላዎቹንም ለመዝጋት ማቀዱን ኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ዘግቧል።
የውጭ ጉዳይ መ/ቤቱ እንዲዘጉ ባቀዳቸው ኤምባሲዎች ይከናወኑ የነበሩ ስራዎችን በአጎራባች ሀገራት ኤምባሲዎች ለማከናወን ማቀዱንም ዘገባው ጠቁሟቋል።
የኤምባሲዎቹና ቆንስላዎቹ መዘጋት የትራምፕ አስተዳደር የፌደራል መንግሥትን ባጀት ለመቀነስ እየወሰደ ያለው እርምጃ አካል ነው ተብሏል።
አሜሪካ ለመዝጋት ካቀደቻቸው አስር ኤምባሲዎች መካከል ስድስቱ በአፍሪካ የሚገኙ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡
በሶማሊያ ሞቃዲሾ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲም ሙሉ በሙሉ እንዲዘጋ፣ ካልሆነ ደግሞ ሰራተኞቹ በከፍተኛ ቁጥር እንዲቀነሱ ሃሳብ መቅረቡን ዘገባው አመላክቷል።
