አሜሪካ ኤርትራ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ልታነሳ ነው !

Date:


የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር፣ አሜሪካ ከኤርትራ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማሻሻል መንገዶችን እያሰላ መሆኑ ተሠማ። የፕሬዝዳንቱ አስተዳደር የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ አማካሪ ማሱድ ቡሎስ፣ የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳደር አሜሪካ በኤርትራ ላይ የጣለቻቸውን የተወሠኑ ማዕቀቦች የማንሳት ሂደት ለመጀመር ፍላጎት እንዳለው ለውጭ ዲፕሎማቶች መናገራቸውን ከባለሥልጣናት መስማቱን ጠቅሶ ዎል ስትሪት ጆርናል ዘግቧል።

ሌሎች ባለሥልጣናት በበኩላቸው፣ አሜሪካ ከኤርትራ ጋር ግንኙነቷን ለማሻሻልና ማዕቀቦችን ለማንሳት የያዘችው እቅድ በግምገማ ሂደት ላይ መሆኑን መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል።

ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ፣ ኤርትራ በፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳደር ሥር ከአሜሪካ ጋር ግንኙነቷን ለማሻሻል ፍላጎት እንዳላት በተደጋጋሚ ሲገልጡ ቆይተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ...

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...