አራት ባንኮች የብሔራዊ ባንክን ‹‹ከባድ›› የብድር ጫና የመቋቋም አቅም ግምገማ ማለፍ አልቻሉም

Date:

የኢትዮጵያ የፋይናንስ ሥርዓት ከፍተኛ የብድር ጫና ቢያጋጥመው አራት ባንኮች በሕግ ከተቀመጠው የካፒታል መጠን በታች እንደሚወርዱና 8.3 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ ካፒታል እንደሚያስፈልጋቸው፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማክሰኞ መጋቢት 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው የፋይናንስ መረጋጋት ሪፖርት ገለጸ።

በፋይናንስ ተቋማት ላይ ሊከሰቱ የሚችሉ የኢኮኖሚ ድንገተኛ ሥጋቶችን የመቋቋም አቅማቸውን የገመገመው ብሔራዊ ባንክ በሪፖርቱ፣ የባንክ ኢንዱስትሪው በአጠቃላይ የተረጋጋ ቢሆንም በአንዳንዶች ላይ ግን በከባድ ሁኔታ ተጋላጭነት መኖሩን አስታውቋል፡፡

‹‹የብድር ሥጋት መቋቋም ግምገማው (Credit Stress Tests) እንደሚያሳየው፣ ሁሉም የንግድ ባንኮች በመካከለኛ ጫና ውስጥ ያለ ምንም ተጨማሪ ካፒታል መደበኛ ሥራቸውን ለመቀጠል የሚያስችል አቅም አላቸው። ሆኖም በከባድ ጫና አራት ባንኮች ፈተናውን ያላለፉ ሲሆን፣ እነዚህም በበጀት ዓመቱ በአጠቃላይ 8.3 ቢሊዮን ብር ወይም ለሥጋት ተጋላጫ ሀብታቸው (Risk Weighted Assets) 1.5 በመቶ የሚሆን ተጨማሪ ካፒታል ያስፈልጋቸዋል፤›› ብሏል።

ይህ የብድር ጫና ግምገማ (Credit Risk Stress Test) የተከናወነው፣ የተበላሹ ብድሮች (NPLs) አሁን ካሉበት ደረጃ በእጅጉ አሻቅበው (Severe) 30 በመቶ ላይ ቢደርሱ ሊፈጠር የሚችለውን ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ ነው።

በብሔራዊ ባንክ ሪፖርት እንደተመላከተው ባንኮች የፋይናንስ ቀውስ በሚፈጠርበት ወቅት…

🔗 ተጨማሪ ያንብቡ: https://ethiopianreporter.com/153613/

ከሪፖርተር

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አርሰናል ከቦርንማውዝ በጉጉት የሚጠበቅ ጨዋታ

በ32ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ቀን...

በአሜሪካ እና ኢራን ድርድር ላይ የሚነሱ አራት ቁልፍ ጥያቄ

በፓኪስታን የሚደረገው የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር እየተጠበበፓኪስታን ነገር ግን...

መንገዳችን ረጅም፣ ጉዟችን ፈታኝ መሆኑን እናውቃለን

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል...

የተመድ ዋና ጸሐፊ ኢራን እና አሜሪካ “በቅን ልቦና” ወደ ድርድሩ እንዲገቡ ጠየቁ

የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አሜሪካ እና ኢራን...