አራት ባንኮች የብሔራዊ ባንክን ‹‹ከባድ›› የብድር ጫና የመቋቋም አቅም ግምገማ ማለፍ አልቻሉም

Date:

የኢትዮጵያ የፋይናንስ ሥርዓት ከፍተኛ የብድር ጫና ቢያጋጥመው አራት ባንኮች በሕግ ከተቀመጠው የካፒታል መጠን በታች እንደሚወርዱና 8.3 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ ካፒታል እንደሚያስፈልጋቸው፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማክሰኞ መጋቢት 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው የፋይናንስ መረጋጋት ሪፖርት ገለጸ።

በፋይናንስ ተቋማት ላይ ሊከሰቱ የሚችሉ የኢኮኖሚ ድንገተኛ ሥጋቶችን የመቋቋም አቅማቸውን የገመገመው ብሔራዊ ባንክ በሪፖርቱ፣ የባንክ ኢንዱስትሪው በአጠቃላይ የተረጋጋ ቢሆንም በአንዳንዶች ላይ ግን በከባድ ሁኔታ ተጋላጭነት መኖሩን አስታውቋል፡፡

‹‹የብድር ሥጋት መቋቋም ግምገማው (Credit Stress Tests) እንደሚያሳየው፣ ሁሉም የንግድ ባንኮች በመካከለኛ ጫና ውስጥ ያለ ምንም ተጨማሪ ካፒታል መደበኛ ሥራቸውን ለመቀጠል የሚያስችል አቅም አላቸው። ሆኖም በከባድ ጫና አራት ባንኮች ፈተናውን ያላለፉ ሲሆን፣ እነዚህም በበጀት ዓመቱ በአጠቃላይ 8.3 ቢሊዮን ብር ወይም ለሥጋት ተጋላጫ ሀብታቸው (Risk Weighted Assets) 1.5 በመቶ የሚሆን ተጨማሪ ካፒታል ያስፈልጋቸዋል፤›› ብሏል።

ይህ የብድር ጫና ግምገማ (Credit Risk Stress Test) የተከናወነው፣ የተበላሹ ብድሮች (NPLs) አሁን ካሉበት ደረጃ በእጅጉ አሻቅበው (Severe) 30 በመቶ ላይ ቢደርሱ ሊፈጠር የሚችለውን ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ ነው።

በብሔራዊ ባንክ ሪፖርት እንደተመላከተው ባንኮች የፋይናንስ ቀውስ በሚፈጠርበት ወቅት…

🔗 ተጨማሪ ያንብቡ: https://ethiopianreporter.com/153613/

ከሪፖርተር

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...