አራት ቤተሰቦቻቸውን በአደጋው አጥተው ለሌሎች መፅናኛ የሆኑት ሊቀመንበር

Date:

አቶ ዳመነ ደበበ የማዞ ዶይሳ ቀበሌ ሊቀመንበር ናቸው። ለበርካቶች መፅናኛ ሆነዋል፤ ምክንያቱም የህዝብ መሪ ናቸውና።

በማዞ ዶይሳ ቀበሌ በተከሰተው አሳዛኝ የመሬት ናዳ አደጋ አቶ ዳመና አራት ቤተሰቦቻቸው ቢያጡም ሕመማቸውን በሆዳቸው ችለው ሌሎችን በማጽናናት የብዙዎችን ትኩረትን ስበዋል።

እኚህ ተወዳጅ ሊቀመንበር መጋቢት 1/2018 ዓ.ም የመጀመሪያው ናዳ ተከስቶ በአካባቢው በብዙዎች ዘንድ ከበሬታ ያላቸውን አቶ “ኤራ የተባሉ አዛውንት ለማትረፍ ህዝቡ “ኤራ አላ ኤራ አላ” እያሉ ሲጮሁ ሰምተው ወደ ስፍራ ለነፍስ አድን ስራ ተገግኝቶ መገኘታቸውን ነግረውናል።

እንደ ህዝብ አገልጋይ አደጋ የደረሰባቸውን ዜጎችን ለማትረፍ ከስፍራዉ የደረሱው ሊቀመንበር ራሳቸው በናዳው ተውጠው በእግዚአብሔር ቸርነት እና በሰው እርብርብ ከተቀበሩበት በተዓምር ወጥተዋል።

በአደጋዉ ባለቤታቸውን፣ ወንድ ልጃቸው እና ልጅ አዝላ የነበረችውን ሴት ልጃቸውን በአጠቃላይ አራት ልጆችን ማጣታቸው የውስጥ ሕመም ሆኖባቸዋል።

በዚህ አስቸጋሪ ጊዜ ለራሳቸው ተጽናንተው ሌሎችን ማበርታት ኃላፊነታቸው ነውና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዶ/ር የተጎዱ ዜጎችን ለማጽናናት ወደ ስፍራው ባቀኑበት ከአንደበታቸው የፈለቀው የመጽናናት መልዕክት ለብዙዎች ብርታት ሆኗል።

ታዲያ እኝህ ብርቱ የሕዝብ አገልጋይ የማዞ ዶይሳ ሕዝብን ለማበርታት ሃዘናቸውን በውስጣቸው ይዘው ሕዝብን በትጋት እያገለገሉ ይገኛሉ።

ዘጋቢ- ዱቡሻ ሚዲያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...