ደራሲ፣አዘጋጅና ተዋናይ ቢኒያም ወርቁ የሚመሰገንበት ልዩ ዝግጅት የፊታችን ሰኞ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ይካሄዳል።
መርሐግብሩ ከሶስት አስርት ዓመታት በላይ በጥበቡ ዓለም የኖረው እና እየኖረ የሚገኘው፣ በርካቶችን ከህልምና ተሰጥኦዋቸው ያገናኘው ሁለገቡ ከያኒ ቢኒያም ወርቁ ለእስካሁን አበርክቶው፣ ትጋትና ብቃቱ በይፋ የሚመሰገንበት መሰናዶ እንደሆነ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
ይህ የምስጋና መርሐግብር የፊታችን ሰኞ መጋቢት 22 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር ከ11 ሰዓት ጀምሮ በተለያዩ ዝግጅቶች ታጅቦ ይከናወናል።
አርቲስት ቢኒያም ወርቁ ከ20 በላይ ፊልሞች እና ከ7 በላይ ትያትሮችን በደራሲነት፣ በአዘጋጅነት፣ በተዋናይነት እና በዳይሬክተርነት ሰርቷል፡፡
