አርቴፊሻል የአካል ድጋፍ የሚሰጡ የሕክምና ባለሙያዎች እጥረት መኖሩ ተገለጸ

Date:

እንደ ሀገር የሰው ሰራሽ የአካል ድጋፍ የሚሰሩ እስፔሻሊስት የሕክምና ባለሙያዎች በከፍተኛ ሁኔታ እጥረት መኖሩን ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

ይህም የሆነበት ምክንያት ለስልጠና የሚወጣው ወጭ ከፍተኛ በመሆኑ ነው ተብሏል።

የጤና ሚኒስቴር የሰው ሀብት ልማት ዘርፍ መሪ ስራ አስፈፃሚ አሰግድ ሳሙኤል ለአሐዱ እንደተናገሩት፤ በተለያየ ሁኔታ አካላቸውን የሚያጡ እና የሰው ሰራሽ የአካል ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች የሚሰሩ እስፔሻሊስት የሕክምና ባለሙያዎች እጥረት ተከስቷል።

ይህን የሕክምና ስልጠና ይሰጥ የነበረው ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እንደነበር ገልጸው በተለያየ ምክንያት የስልጠና ሂደቱ ተቋርጦ መቆየቱን አስታውቀው በአሁኑ ጊዜ ሕክምናውን ለማድረግ በተለያየ ምክንያት ፍላጎቱ እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል።

የተገልጋዩ ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የስልጠና ሂደቱን መጀመሩን አቶ አሰግድ ተናግረዋል።

ችግሩን ለመፍታት በክልል ደረጃ ስልጠናውን ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነ አንስተው፤ የሚሰለጥኑ የሕክምና ባለሙያዎች የምልመላ ሂደትም መጠናቀቁን ገልጸዋል።

የጤና ስልጠና በፍላጎት ላይ የተመሰረተ ሲሆን፤ በየ ጤና ተቋሙ የሚሰጠው አገልግሎት የተለያየ መሆኑን ተጠቁሟል፡፡

የጤና ሚኒስቴር ለጤና ባለሙያዎች ለሚሰጠው ስልጠና የበጀት እጥረት እና የሎጅስቲክ ችግር እየገጠመው መሆኑንም ሥራ አስፈጻሚው ጨምረው አስታውቀዋል።

የተፈጠረው የበጀት ችግር ለመፍታት በማህበራዊ ትስስር ስልጠና እየሰጠ ቢሆንም፤ የግድ በአካል ስልጠና መስጠት ሲፈልግ ችግር እንደሆነበት አስታውቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...