አትሌት ጌታነህ የ10 ኪሎ ሜትር ሩጫ ውድድር  አሸናፊ ሆነ

Date:

አትሌት ጌታነህ ሞላ  በቢሾፍቱ ከተማ በተካሄደው የአየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ በዓል የ10 ኪሎ ሜትር ሩጫ አሸናፊ ሆኗል።
የኢፌዴሪ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በተለያዩ ዝግጅቶች እያከበረ ይገኛል።

የምስረታ በዓሉ አካል የሆነው ቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ እየተካሄደ ነው።

በጎዳና ላይ ሩጫው ከጎረቤት ሀገራት ጭምር አትሌቶች  ተሳታፊ ሆነዋል።
በሩጫው በሁለቱም ጾታዎች ለሚያሸንፉ ተወዳዳሪዎች በተመሳሳይ 500 ሺህ ብር ሽልማት ይበረከትላቸዋል።

ሁለተኛ ደረጃን  ይዘው ለሚያጠናቅቁ 250 ሺህ ብር፣ ሶስተኛ ደረጃ ለሚወጡ 100 ሺህ ብር፣ አራተኛ ለሚወጡ 50 ሺህ ብር እና አምስተኛ ለሚወጡ አትሌቶች የ25 ሺህ ብር ሽልማት እንደሚበረከትላቸውም ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...