የ2026 የዓለም የብስክሌት ኤሊሚኔተር ፕሮ ሊግ የመክፈቻ ውድድር መጋቢት 20, 2018 በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
ይህ ውድድር በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄድ ዓለም አቀፍ የከተማ ውስጥ የብስክሌት ውድድር ይሆናል ተብሏል።
በውድድሩ ዓለም አቀፍ ፕሮፌሽናል ተወዳዳሪዎች በሁለቱም ጾታ ይሳተፉበታል ተብሎ ይጠበቃል።
የዚህ ውድድር አዘጋጅ መቀመጫውን ቤልጂየም ያደረገው ሲቲ ማውንቴን ባይክ (City Mountainbike) ነው
ውድድሩ ምን አንነት መልክ አለው ?
ኤሊሚኔተር (XCE) የተባለው ይህ የብስክሌት ውድድር ዘርፍ፣ ተወዳዳሪዎች በከተማ መሃል በተዘጋጁ አጫጭርና ሰው ሰራሽ መሰናክሎች በሚገኙባቸው መንገዶች ላይ በከፍተኛ ፍጥነት የሚፎካከሩበት ነው።
በአንድ ጊዜ 4 ተወዳዳሪዎች አብረው የሚለቀቁ ሲሆን ውድድሩ በጣም አጭርና ፈጣን ነው።
መጀመሪያ የደረሱት ሁለቱ ተወዳዳሪዎች ወደ ቀጣዩ ዙር ያልፋሉ፤ የመጨረሻዎቹ ሁለቱ ግን ከውድድሩ ይሰናበታሉ። ይህ ሂደት አንድ አሸናፊ እስኪቀር ድረስ ይቀጥላል።
የአዲስ አበባው ውድድር እንደተጠናቀቀ የውድድር ዘመኑ ቀጣይ ዙር በታጂኪስታን ዱሻንቤ ከተማ የሚቀጥል ይሆናል ተብሏል።
