ኢራን ሚሳይል የማስወንጨፍ አቅሟን ከጦርነቱ በፊት ከነበረው “በበለጠ ፍጥነት” እየገነባች መሆኑን ገለፀች

Date:

የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ከፍተኛ አዛዥ፤ አገሪቱ ሚሳይል እና ሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) የማስወንጨፊያ መሠረተ ልማቶቿን አሁን ባለው የተኩስ አቁም ወቅትም ጭምር ከጦርነቱ በፊት ከነበረው በበለጠ ፍጥነት እያደራጀች መሆኑን ገለጹ።

ኑር ኒውስን ዋቢ አድርጎ አልጀዚራ እንደዘገበው፤ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ የኤሮስፔስ ክፍል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ማጂድ ሙሳቪ የኢራን የማስወንጨፊያ ስርዓቶች መልሶ ግንባታ እና የማዘመን ሂደት መፋጠኑን ተናግረዋል።

ጄኔራል ሙሳቪ ከመሬት በታች የሚገኝ የሚሳይል ተቋምን በሚጎበኙበት ወቅት በሰጡት አስተያየት፤ “በተኩስ አቁም ወቅት የሚሳይል እና የድሮን ማስወንጨፊያዎችን የማዘመን እና የመተካት ፍጥነታችን ከጦርነቱ በፊት ከነበረውም የላቀ ነው” ብለዋል።

አዛዡ የኢራንን አቋም ከተቃዋሚዎቿ ጋር በማነፃፀር፤ “ባላንጣዎቻችን የጦር መሣሪያ ክምችታቸውን እንደ እኛ በፍጥነት መልሰው መገንባት አልቻሉም” ያሉ ሲሆን፣ ባላንጣዎቻቸው አሁንም በውጭ እርዳታ ላይ ጥገኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ሙሳቪ አክለውም ኢራን እና አጋሮቿ በግጭቱ የበላይነት ማግኘታቸውን፤ በሆርሙዝ የባሕር ሰርጥ፣ በሊባኖስ እና በአጠቃላይ በቀጠናው ያለውን ሁኔታ በማንሳት “በዚህኛው የጦርነት ምዕራፍ ተሸንፈዋል” ሲሉ ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚያደርጉት ድርድር እስኪጠናቀቅ ድረስ የተኩስ አቁሙ መራዘሙን አስታወቁ

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፓኪስታን ጥያቄ መሠረት ከኢራን ጋር የገቡትንየተኩስ...

ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የሚውል የ40 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ተፈቀደ

የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የልማት ክንፍ የሆነው ኢአይቢ ግሎባል (EIB...

ሃይንከን በአልኮል መጠኑ ጠንከር ያለ ቢራ ለኢትዮጵያ ገበያ አስተዋወቀ

ሃይንከን ኢትዮጵያ በእለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ የሆነውን ዴሰፔራዶስ (Desperados)...