ኢራን በሆርሙዝ ወሽመጥ ሊያልፍ የነበረ ነዳጅ ጫኝ መርከብ መምታቷን አስታወቀች

Date:

አብዮታዊ ዘቡ በቴሌግራም ቻናሉ ባወጣው መረጃ፤ “ፕሪማ” የሚል ስያሜ ያለው ነዳጅ ጫኝ መርከብ በወሽመጡ በኩል “መተላለፍ እንደማይቻል” በባሕር ኃይሉ የተሰጠውን “ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ችላ በማለቱ በድሮን መመታቱን ገልጿል።

“ከጠበኛ አገራት ጋር አጋር የሆኑ” ነዳጅ ጫኝ እና የንግድ መርከቦች በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል ማለፍ እንደማይፈቀድላቸውም ወታደራዊ ኃይሉ አስገንዝቧል።

በዓለም ላይ ካሉ ወሳኝ የኃይል ማጓጓዣ መስመሮች አንዱ የሆነው የሆርሙዝ ወሽመጥ፤ ከዓለም አቀፉ የነዳጅ እና ጋዝ አቅርቦት አንድ አምስተኛ የሚሆነው ይተላልፍበታል።

በመካከለኛው ምሥራቅ እየተካሄደ ያለው ጦርነት የመርከብ መተላለፊያ መስመሩ ሙሉ እንዲቆም አድርጎታል።

በዚህ ሳምንት መጀመሪያ የኢራን መንግሥት በመስመሩ ለመተላለፉ የሚሞክሩ መርከቦችን “በእሳት እንደሚያያይዝ” ዝቷል።

ኢራን ይህንን ካለች በኋላ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ “አስፈላጊ ከሆነ” የአሜሪካ ባሕር ኃይል በዚያ የሚያልፉ መርከቦችን እንደሚያጅብ ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አርሰናል ከቦርንማውዝ በጉጉት የሚጠበቅ ጨዋታ

በ32ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ቀን...

በአሜሪካ እና ኢራን ድርድር ላይ የሚነሱ አራት ቁልፍ ጥያቄ

በፓኪስታን የሚደረገው የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር እየተጠበበፓኪስታን ነገር ግን...

መንገዳችን ረጅም፣ ጉዟችን ፈታኝ መሆኑን እናውቃለን

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል...

የተመድ ዋና ጸሐፊ ኢራን እና አሜሪካ “በቅን ልቦና” ወደ ድርድሩ እንዲገቡ ጠየቁ

የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አሜሪካ እና ኢራን...