ኢራን ወደ ውይይት ካልተመለሰች የኃይል ማመንጫዎቿ እና ድልድዮቿ እንደሚመቱ ትራምፕ አስጠነቀቁ

Date:

ኢራን ወደ ውይይት ካልተመለሰች የኃይል ማመንጫዎቿ እና ድልድዮቿ ላይ በቀጣይ ሳምንት ጥቃት እንደሚሰነዘር ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስጠነቀቁ።

ትራምፕ ይህንን ያሉት ከፎክስ ኒውስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ሲሆን፤ በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች 20% ክፍያ እንዲፈጽሙ ያቀረቡትን ሐሳብም ሰርዘዋል።

ትራምፕ በኢራን ወደቦች ላይ የጣሉት እገዳ ግን ባለበት እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

“በቀጣይ ሳምንት ነገሮች የከፉ ይሆኑባቸዋል። ወደ ድርድር ጠረጴዛው የማይመለሱ ከሆነ የኃይል ማመንጫዎቻቸውን እናፈርሳለን፤ ድልድዮቻቸውን እናፈርሳለን” ብለዋል።

የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ባለሥልጣን ቮልከር ቱርክ የትራምፕን ዛቻ ኮንነዋል።

ትራምፕ በኢራን የሲቪሎች መሠረተ ልማት ላይ ጥቃት ለማድረስ መዛታቸው “በዓለም አቀፍ ሕግ የተከለከለ” መሆኑን ገልጸዋል።

“ሆነ ብሎ ንጹኃን ዜጎች ላይ እና መሠረተ ልማት ላይ ጥቃት መፈጸም የጦር ወንጀል ነው” በማለትም አክለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጄኤፍኤም 106.7 የሬዲዮ ጣቢያ ለ6 ወራት ታገደ

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባደረገው የይዘት ክትትልና የኢንስፔክሽን ምልከታ...

ሱልጣን ቢን ኻሊፋ ግሩፕ በኢትዮጵያ በሆቴል ዘርፍ ሊሰማራ ነው

በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች የኢፌዲሪ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር...

የአሜሪካ የታክስ ህግ የስፔንን የዓለም ዋንጫ ሽልማት ስጋት ላይ ጣለ

የስፔን ብሔራዊ ቡድን ከዓለም ዋንጫ ሊያገኘው ከሚችለው 50 ሚሊዮን...

ህወሓት ከሌሎች ተቃዋሚ ኃይሎች ጋር የሚደረግ ጥምረት አስፈላጊ መሆኑን ገለጸ

ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ...