ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ልታካሂድ ነው

Date:

ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ መላ አገሪቱን የሚያዳርስ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ለማካሄድ ዝግጅት እያደረገች ነው። የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በ2018 ዓ.ም. ለሚካሄደው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጀመሩን ይፋ አድርጓል።

ይህ ቆጠራ ከመስከረም ወር ጀምሮ በመላው አገሪቱ ከትናንሽ እስከ ትላልቅ የምርትና የንግድ ድርጅቶች ላይ የሚካሄድ በመሆኑ፣ በየደረጃው ያለው የመንግሥት አደረጃጀት፣ የኢኮኖሚ ድርጅት ባለቤቶች እንዲዘጋጁ ተጠይቋል።

የቅድመ ዝግጅት ተግባራት የቆጠራውን ስነ ዘዴ ማዘጋጀት፣ የሰው ኃይል ማሰልጠን፣ ለመስክ ሥራ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ማሟላትና የቴክኖሎጂ ዝግጅትን ማካተት እንደሚያጠቃልል ከተቋሙ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የቦርድ አባላትን ሹመት አጸደቀ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የቦርድ አባላትን...

የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን በሀገር-በቀል አቅም ለማጠናከር የሚያስችል ግብረ ኃይል ተቋቋመ

የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በሀገር ውስጥ አቅም ላይ...

ዶናልድ ትራምፕ የ’ICE’ ተቋምን ስም ወደ ‘NICE’ ለመቀየር መወሰናቸው አነጋጋሪ ሆነ

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሀገሪቱ የኢሚግሬሽን እና የጉምሩክ አስከባሪ...

የአዲስ አፍሪካ ሪል እስቴት ኤክስፖ የአራት ቀናት ስኬታማ የሥራ ክንውን

በኢትዮጵያ የሪል እስቴት አልሚዎች ማኅበር ባለቤትነት እንዲሁም በከተማ መሠረተ...