“ኢትዮጵያ በአመት የማር ምርት 10 በመቶውን ብቻ ነው የምታመርተው”-  ጥናት

Date:

ኢትዮጵያ በአመት የማር ምርት የማምረት አቅሟ 500 ሺህ ቶን ቢሆንም በዘርፉ ባሉ ተግዳሮቶች 10 በመቶውን ብቻ እንደምታመርት አንድ ጥናት አመላከተ።

ጥናቱን ያጠኑት በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት መሪ ተመራማሪ እና የእንስሳት ፖሊሲ ምርምር ዘርፍ ሃላፊ የሆኑት ዶክተር ደሳለኝ ቤኛ ሲሆኑ 22 የዘርፉ ተዋናኞች ተካተውበታል።

ዶክተር ደሳለኝ ቤኛ በኢትዮጵያ የንብ አረባቡ እና አመራረቱ 92 በመቶ የሚካሄደው በባህላዊ ዘዴ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ዶክተር ደሳለኝ ቤኛ በዝርዝር ምን አሉ ?

የዓለም የማር ፍላጎት እየጨመረ ቢመጣም ኢትዮጵያ ጥራት ባለው የግብአት አቅርቦት ውስንነት፣ በቂ መሠረተ ልማት ባለመሟላቱ እና ለንብ አናቢዎች በቂ ሥልጠና ባለመሰጠቱ ማምረት ከሚገባት በጣም ዝቅተኛ እያመረተች ትገኛለች።

ደረጃቸውን የጠበቁ የምርት ጥራት ማረጋገጫ ዘዴዎች አለመኖራቸው በዓለም ገበያ ያላትን ተወዳዳሪነትም በእጅጉ እየጎዳው ነው።

በጥናቱ ማረጋገጥ እንደተቻለው የምናመርትበት ቴክኖሎጅ የችግሩ መንስኤ ነው። የንብ አረባቡ እና አመራረቱ 92 በመቶ የሚኣሄደው በባህላዊ ዘዴ ነው። ይህ ደግሞ ለአመራረት ምቹ አይደለም።

ምክንያቱ ደግሞ ማሩ ሲቆረጥ የሞቱ ንቦች አብረው ይቀላቀላሉ፣ የማሩ እንጀራ እና  ማሩ አንድ ላይ ይሰባበራል። ጥራቱንም በእጅጉ እየጎዳው ነው።

ለማምረቻ እና ለምርት ውጤቶች የሚሆኑ የግብአት አቅርቦት የለም፣ ያሉትም ጥራታቸው ከፍተኛ ችግር አለበት።

ምርቱም ምግብ ነክ በሆኑ እና ባልሆኑ እንደ ስኳር ባሉ ነገሮች እየተከለሰ ለገበያ እየቀረበ ነው። በጥራት ጉድለት ላኪዎችም በአለም አቀፍ ገበያው ላይ ተወዳዳሪ አለመሆናቸውን በግልፅ አስቀምጧል።

በዘርፉ የተሰማሩ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጀቶች የራሳቸውን ፕሮጀክት አላማ ወይም ሪፖርታቸውን ለማሳካት ብቻ ነው የሚሰሩት። ይህ ደግሞ ዘርፉን እየፈተነው ነው።

የአረባብ ዜዴውን ማዘመን፣ ለአምራቾች የቴክኖሎጅ አጠቃቀምን ማስተማር፣ የፀረ ተባይ ኬሚካሎችን አጠቃቀም ግንዛቤ መስጠት፣ በዘርፉ ያሉ ፖሊሲዎች ተግባራዊ የሚሆኑበትን ሁኔታ መፍጠር አስፈላኪ መሆኑን ገልፀዋል።

የላኪዎችን አቅም ማሳደግ እና ምቹ ሁኔታ መፍጠር፣ አርሶ አደሮችን በማሰባስብ እንድያመርቱ ማድረግ፣ የማር ምረት መያዣ እቃዎችን ጥራት ማሳደግ፣ ባለሀብቶችን ወደ ዘርፉ ማምጣት ለችግሮቹ መፍትሄ መሆኑን ጠቁመዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...