በጀርመን የኢትዮጵያ አምባሳደር እስክንድር ይርጋ ከጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሰሃራ በታች አገራት እና ሳሄል ዳይሬክተር አምባሳደር ክርስቶፍ ሬትዝላፍ ጋር ዛሬ ውይይት አድርገዋል።
ውይይቱ የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ማጠናከርን ያለመ ነው።
ሀገራቱ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙታቸውን የጀመሩበት 120ኛ ዓመት በጋራ በሚያከብሩበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውንም በበርሊን የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያ እና ጀርመን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1905 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።
ሁለቱ ሀገራት በየሀገራቱ ኤምባሲያቸውን የከፈቱት እ.አ.አ በ1907 ነው።
ግብርና፣ ምግብ ዋስትና፣ ትምህርት፣ ማህበራዊ ዋስትና እና የግሉ ዘርፍ አቅም ግንባታ ከኢትዮ-ጀርመን የትብብር መስኮቹ መካከል ይጠቀሳሉ።
