ኢትዮጵያ እና ጀርመን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩበትን 120ኛ ዓመት ያከብራሉ

Date:

በጀርመን የኢትዮጵያ አምባሳደር እስክንድር ይርጋ ከጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሰሃራ በታች አገራት እና ሳሄል ዳይሬክተር አምባሳደር ክርስቶፍ ሬትዝላፍ ጋር ዛሬ ውይይት አድርገዋል።

ውይይቱ የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ማጠናከርን ያለመ ነው።

ሀገራቱ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙታቸውን የጀመሩበት 120ኛ ዓመት በጋራ በሚያከብሩበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውንም በበርሊን የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

ኢትዮጵያ እና ጀርመን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1905 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።

ሁለቱ ሀገራት በየሀገራቱ ኤምባሲያቸውን የከፈቱት እ.አ.አ በ1907 ነው።

ግብርና፣ ምግብ ዋስትና፣ ትምህርት፣ ማህበራዊ ዋስትና እና የግሉ ዘርፍ አቅም ግንባታ ከኢትዮ-ጀርመን የትብብር መስኮቹ መካከል ይጠቀሳሉ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባኦት ቅድስት...

በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም ዓይናቸው በጽኑ መታመሙን ጠበቃቸው ገለጹ

ከሁለት ዓመት በላይ በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም አበራ...

ንግድ ባንክ “ስታርፔይ” የተሰኘ አዲስ መተግበሪያ ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንክ ሥርዓቱን ይበልጥ ዘመናዊና ቀልጣፋ...

በኢትዮጵያ በካንሰር ከሚያዙ ሕፃናት መካከል 75 በመቶ የሚሆኑት ህክምና አያገኙም

በኢትዮጵያ በየዓመቱ በካንሰር ከሚጠቁ ከ6 ሺህ እስከ 8 ሺህ...