ኢትዮጵያ እና ጀርመን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩበትን 120ኛ ዓመት ያከብራሉ

Date:

በጀርመን የኢትዮጵያ አምባሳደር እስክንድር ይርጋ ከጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሰሃራ በታች አገራት እና ሳሄል ዳይሬክተር አምባሳደር ክርስቶፍ ሬትዝላፍ ጋር ዛሬ ውይይት አድርገዋል።

ውይይቱ የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ማጠናከርን ያለመ ነው።

ሀገራቱ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙታቸውን የጀመሩበት 120ኛ ዓመት በጋራ በሚያከብሩበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውንም በበርሊን የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

ኢትዮጵያ እና ጀርመን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1905 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።

ሁለቱ ሀገራት በየሀገራቱ ኤምባሲያቸውን የከፈቱት እ.አ.አ በ1907 ነው።

ግብርና፣ ምግብ ዋስትና፣ ትምህርት፣ ማህበራዊ ዋስትና እና የግሉ ዘርፍ አቅም ግንባታ ከኢትዮ-ጀርመን የትብብር መስኮቹ መካከል ይጠቀሳሉ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...

ኧረ ፋታ ስጡን?!

መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው :: አጀንዳ...