ኢትዮጵያ የብሪክስ ባንክን ለመቀላቀል የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶችን ድጋፍ ጠየቀች

Date:

ኢትዮጵያ የብሪክስ አዲስ ልማት ባንክ አባል ለመሆን በምታደርገው ጥረት የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶችን ድጋፍ በይፋ ጠየቀች።

በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች የኢትዮጵያ አምባሳደር ዑመር ሁሴን በዚሁ ጉዳይ ላይ በቅርቡ በሀገሪቱ የፋይናንስ ሚኒስቴር የዓለም አቀፍ የፋይናንስ ግንኙነት ዳይሬክተርና የባንኩ ተወካይ ከሆኑት ቱራዬያ አልሃሺሚ ጋር ተወያይተዋል።

በውይይታቸው ወቅት አምባሳደር ዑመር ሁሴን ኢትዮጵያ የባንኩ አባል ለመሆን ያላትን ፍላጎትና እየተደረጉ ያሉትን ጥረቶች በዝርዝር ገልጸዋል። በተለይም ኢትዮጵያ ለተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ያላትን ወዳጅነት በመጥቀስ ለአባልነት ጥያቄያቸው አዎንታዊ ምላሽ እንዲሰጡላቸው ጠይቀዋል። የኢትዮጵያ ኤምባሲም ይህንኑ መረጃ አረጋግጧል።

የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ራሷ እ.አ.አ ጥቅምት 4 ቀን 2021 የብሪክስ አዲስ ልማት ባንክን መቀላቀሏ አይዘነጋም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አርሰናል ከቦርንማውዝ በጉጉት የሚጠበቅ ጨዋታ

በ32ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ቀን...

በአሜሪካ እና ኢራን ድርድር ላይ የሚነሱ አራት ቁልፍ ጥያቄ

በፓኪስታን የሚደረገው የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር እየተጠበበፓኪስታን ነገር ግን...

መንገዳችን ረጅም፣ ጉዟችን ፈታኝ መሆኑን እናውቃለን

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል...

የተመድ ዋና ጸሐፊ ኢራን እና አሜሪካ “በቅን ልቦና” ወደ ድርድሩ እንዲገቡ ጠየቁ

የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አሜሪካ እና ኢራን...