ኤምባሲዎችና የውጭ ባለሀብቶች በ«ፍራንኮ-ቫሉታ» ነዳጅ እንዲያስገቡ ተፈቀደ

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ኤምባሲዎች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና የውጭ ቀጥተኛ ባለሀብቶች በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ (በፍራንኮ-ቫሉታ) ነዳጅ እንዲያስገቡ የሚፈቅደውን አዲስ መመሪያ ተግባራዊ አድርጓል።

በማዕከላዊ ገዢው እዮብ ተካልኝ ፊርማ ባለፈዉ ሳምንት የጸደቀው ይህ መመሪያ፣ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ፍላጎት በማቃለል የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ለመፍጠር ያለመ ሲሆን፤ የሚገባው ነዳጅ ለተቋማቱ የራስ አገልግሎት ብቻ እንዲውል፣ ለንግድ እንዳይቀርብ እና በዲጂታል ሥርዓት በጥብቅ እንዲከታተል ይደነግጋል።

ባለፉት ዓመታት የነዳጅ ምርቶችን ወደ ሀገር ውስጥ በብቸኝነት የማስገባት መብት የነበረው የመንግሥት ይዞታ ለሆነው ለኢትዮጵያ የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ነበር። ይሁን እንጂ ነዳጅ የሀገሪቱ ትልቁ የገቢ ምርት መሆኑ እና የውጭ ምንዛሬ እጥረት መኖሩ አቅርቦቱ ላይ ተጽዕኖ ፈጥሮ ቆይቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...