የእስራኤል ጦር በማዕከላዊ ጋዛ ዲር አል ባላህ ላይ የምድር እና የአየር ጥቃት ሰንዝራለች፡፡
እስራኤል ከሃማስ ጋር ባካሄደችው የ21 ወራት ጦርነት ከዚህ በፊት የምድር ጥቃት አልጀመረችም ነበር።
አካባቢው በደቡባዊ ጋዛ ከራፋህ እና ካን ዮኒስ በተፈናቀሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተሞልቷል።
በአካባቢው የእስራኤል ታጋቾች እየተያዙ እንደሆነም ተገልጾል፡፡
የእስራኤል ዘመቻ የጀመረው ዛሬ ጠዋት ሲሆን ነዋሪዎች እንደገለጹት ታንኮች እና ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች በከባድ መሳሪያ እና በአየር ሽፋን ወደ ከተማዋ ገብተዋል።
