እስራኤል ኢራንን ልታጠቃ እንደምትችል በመነገሩ የነዳጅ ዘይት ዋጋ ጨመረ

Date:

እስራኤል በኢራን የኒውክሌር ኃይል ላይ ጥቃት ለመፈፀም መዘጋጀቷን ተከትሎ የነዳጅ ዋጋ ከ1 በመቶ በላይ ጨምሯል።

የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ የሀምሌ ወር ዋጋ 68 ሳንቲም ወይም 1.04 በመቶ ከፍ ብሏል።

በዩናይትድ ስቴትስ የዌስት ቴክሳስ መካከለኛ የሀምሌ ወር የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ የወደፊት እጣ 70 ሳንቲም ወይም 1.1 በመቶኛ ጨምሮ ወደ 62.73 ዶላር ከፍ ብሏል።

በዩናይትድ ስቴትስ የተገኘ አዲስ መረጃ እስራኤል የኢራንን የኒውክሌር መስሪያ ቤቶችን ለመምታት በዝግጅት ላይ መሆኗን ሲኤንኤን ጉዳዩን ከሚያውቁ በርካታ የአሜሪካ ባለስልጣናትን ጠቅሶ ዘግቧል።

ባለሥልጣኖቹን ጠቅሶ ሲ ኤን ኤን አክሎ እንደዘገበው የእስራኤል መሪዎች ጥቃት ለመፈፀም የመጨረሻ ውሳኔ ማድረጋቸው ግልጽ አይደለም ብለዋል።

“እንዲህ ዓይነቱ የውጥረት መባባስ የኢራንን የነዳጅ አቅርቦትን አደጋ ላይ የሚጥል ብቻ ሳይሆን በሰፊው ሰፊው ክልል ውስጥም ጭምር አደጋ የሚደቅን ነው” ሲሉ የሸቀጦች ስትራቴጂስቶች ገልፀዋል።

ኢራን በፔትሮሊየም ላኪ አገሮች ድርጅት ውስጥ በሦስተኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ ሲሆን የእስራኤል ጥቃት ከአገሪቷ የሚመጡትን የነዳጅ ፍሰት ሊረብሽ ይችላል።

በተጨማሪም ኢራን በባህረ ሰላጤው በሆርሙዝ ማለፊያ በኩል የሚተላለፈውን የነዳጅ ጫኝ በመዝጋት አፀፋውን ልትመልስ ትችላለች የሚል ስጋት አለ በዚህም ሳዑዲ አረቢያ ኩዌት ኢራቅ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ድፍድፍ ዘይት እና ነዳጅ ወደ ውጭ መላክ እንዳይችሉ ያደርጋል።

ዳጉ_ጆርናል

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...