የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር ኢዝራኤል ካትዝ በኢራን የፔትሮኬሚካል ማምረቻ ፋብሪካ ላይ ድብደባ መፈጸሙን ገለጹ።
ሚኒስቴሩ አክለውም ጦሩ “በሙሉ ኃይሉ” የኢራን መሠረተ ልማቶች ላይ ጥቃት መፈጸሙን እንዲቀጥል ታዝዟል ብለዋል።
“የእስራኤል መከላከያ በኢራን ግዙፉ የሆነውን እና [በአሳሉያህ] የሚገኘውን የፔትሮኬሚካል ፋብሪካ ላይ ከባድ ጥቃት ፈጽሟል ብለዋል።
ባለፈው ሳምንት በተመሳሳይ መልኩ በሌላ ፋብሪካ ላይ ጥቃት መፈጸሙን ጨምረው ገልጸዋል።
“ለኢራን የፔትሮኬሚካል የውጭ ንግድ በጥምረት 85 በመቶ አስተዋጽኦ የሚያደርጉት ሁለቱ ፋብሪካዎች ከጥቅም ውጭ ተደርገዋል ስለዚህ አገልግሎት አይሰጡም” ሲሉ በመግለጫቸው ላይ ተናግረዋል።
ካትዝ አክለውም በአሳሉያህ የሚገኘው ፋብሪካ የአገሪቱን ግማሽ የፔትሮኬሚካል ምርቶች የሚያመርት ነበር ብለዋል።
ታስኒም የዜና ወኪል በበኩሉ ሁለት የፔትሮኬሚካል ኩባንያዎች ላይ ጥቃት መፈጸሙን ዘግቧል።
ካትዝ የኢራን ፔትሮኬሚካል ፋብሪካ ላይ ጥቃት መፈጸሟን የገለጹት የፋርስ የዜና ወኪል በአሳሉያህ ከሚገኘው በሳውዝ ፓርስ ፔትሮኬሚካል ፋብሪካ ብዙ ፍንዳታዎች መሰማታቸውን ከዘገበ በኋላ ነው።
