በጅቡቲ ሶስት የነዳጅ ጫኝ መርከቦች መድረሳቸው ተነገረ

Date:

አይኤምኤፍ ግን የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት በባህረ ሰላጤው ውጥረት ምክንያት ለችግር ተጋልጠው እንደሚቀጥሉ አስጠነቀቀ

​በጅቡቲ ወደብ ሦስት ግዙፍ የነዳጅ ጫኝ መርከቦች መድረሳቸው የተሰማ ሲሆን፣ ይህም በኢትዮጵያ ለተከሰተው የነዳጅ እጥረት መጠነኛ እፎይታ ሊሰጥ እንደሚችል ተስፋ ተጥሎበታል።

ከመጋቢት 19 እስከ 23 ባሉት ጊዜያት ዉስጥ በጅቡቲ የደረሱት እነዚህ መርከቦች በአጠቃላይ 143,000 ሜትሪክ ቶን የሚመዝን ናፍጣና የጄት ነዳጅ የጫኑ መሆናቸውን ካፒታል ለመረዳት ችሏል።

​ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት በባህረ ሰላጤው አካባቢ ባለው ውጥረት ምክንያት አሁንም ለከፍተኛ የኢኮኖሚ ችግር ተጋልጠው እንደሚቀጥሉ አስጠንቅቋል።

እንደ አይኤምኤፍ ትንታኔ ከሆነ፣ በባህረ ሰላጤው የሚታየው አለመረጋጋት የንግድ ልውውጥን በማስተጓጎልና የጭነት ዋጋን በመጨመር በቀጣናው ሀገራት ላይ የዋጋ ንረትን ሊያስከትል ይችላል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...