እጅጋየሁ ታዬ ሻምፒዮን ሆነች

Date:

በጃማይካ ኪንግስተን በተደረገው የ5 ሺህ ሜትር ረጅም ርቀት ግራንድ ስላም ትራክ አትሌት እጅጋየሁ ታዬ በበላይነት አጠናቃለች።

14 ደቂቃ 54.88 ሰከንድ እጅጋየሁ ርቀቱን ለማጠናቀቅ የወሰደባት ጊዜ ሆኗል።

ቀደም ብላ የ3 ሺህ ሜትር ረጅም ርቀትን በተመሳሳይ በአንደኝነት ያጠናቀቀችው አትሌቷ
ያገኝችውን ነጥብ 24 በማድረስ የርቀቱ ሻምፒዮን ሆናለች።

በመሆኑም በአዲሱ ውድድር የአለም ሻምፒዮና የነሀስ ሜዳልያ ባለቤቷ አትሌት እጅጋየሁ ታዬ የ100 ሺህ ዶላር ተሸላሚ ሆናለች።

ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ጽጌ ገብረሰላማ 3ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።

ጽጌ በ3 ሺህ ሜትር ረጅም ርቀት በተመሳሳይ 3ኛ ሆና ማጠናቀቋ የሚታወስ ሲሆን ያገኝችውን ነጥብ 12 በማድረስ የ30 ሺህ ዶላር ተሸላሚ ሆናለች።

ኬንያዊቷ አግነስ ኒጌቲች ደግሞ በአጠቃላይ የረጅም ርቀት ውጤት 2ኛ ወጥታለች።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የዲጂታል ኢትዮጵያን ጉዞ ላይ የጋራ ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ ሥልጠና አከናወነ

ኩባንያችን ከመንግሥት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጋር በመተባበር...

የኔታንያሁ ድንገተኛ ማስጠንቀቂያ እና የቢሊዮን ዶላር የጋዝ ሚስጥር!

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ከታሪካዊቷ የግብፅ ምድር የሚሰማው...

ኤርትራ ሠራዊቷን በአስቸኳይ ከግዛቷ እንድታስወጣ እና ለድርድር ዝግጁ እንድትሆን ኢትዮጵያ ጠየቀች

የኤርትራ ሠራዊት ተቆጣጣሯቸዋል ካላቸው የኢትዮጵያ ሉዓላዊ ግዛቶች እንዲወጣ እና...

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የደንበኞች ቁጥሩ ከ5.46 ሚሊየን በላይ መድረሱን ገለፀ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የ2018 አ.ም የስድስት ወር የዕቅድ አፈፃፀሙን...