እጅጋየሁ ታዬ ሻምፒዮን ሆነች

Date:

በጃማይካ ኪንግስተን በተደረገው የ5 ሺህ ሜትር ረጅም ርቀት ግራንድ ስላም ትራክ አትሌት እጅጋየሁ ታዬ በበላይነት አጠናቃለች።

14 ደቂቃ 54.88 ሰከንድ እጅጋየሁ ርቀቱን ለማጠናቀቅ የወሰደባት ጊዜ ሆኗል።

ቀደም ብላ የ3 ሺህ ሜትር ረጅም ርቀትን በተመሳሳይ በአንደኝነት ያጠናቀቀችው አትሌቷ
ያገኝችውን ነጥብ 24 በማድረስ የርቀቱ ሻምፒዮን ሆናለች።

በመሆኑም በአዲሱ ውድድር የአለም ሻምፒዮና የነሀስ ሜዳልያ ባለቤቷ አትሌት እጅጋየሁ ታዬ የ100 ሺህ ዶላር ተሸላሚ ሆናለች።

ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ጽጌ ገብረሰላማ 3ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።

ጽጌ በ3 ሺህ ሜትር ረጅም ርቀት በተመሳሳይ 3ኛ ሆና ማጠናቀቋ የሚታወስ ሲሆን ያገኝችውን ነጥብ 12 በማድረስ የ30 ሺህ ዶላር ተሸላሚ ሆናለች።

ኬንያዊቷ አግነስ ኒጌቲች ደግሞ በአጠቃላይ የረጅም ርቀት ውጤት 2ኛ ወጥታለች።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ትራምፕ የኢራን የኒውክሌር ተቋም ላይ ጥቃት ለማድረስ ዛቱ

አሜሪካ በኢራን ላይ የምታደርሰው ጥቃት 11ኛ ቀኑን ይዟል። ፕሬዝዳንት...

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአሜሪካ ” American Space ” ማዕከል ተመረቀ

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቨን ማሲንጋ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተቋቋመውን "American...

አሐዱ ባንክ ለ 8ኛ ጊዜ የደም ልገሳ መርሐ ግብር አከናወነ

አሐዱ ባንክ ሥራ የጀመረበትን 4ኛ ዓመት በማስመልከት የተለያዩ ኩነቶችን...

ዕንባ ጠባቂ ከቀረቡለት አቤቱታዎች 84% በመንግስታዊ ተቋማት ላይ የቀረቡ ናቸው

የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በተጠናቀቀው የ2018 በጅት ዓመት...