ከአንድ ተቋም የተባረረ ተማሪ የቀድሞ ውጤቱ አይያዝለትም

Date:

የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በአካዳሚክ  ምክንያት ለተባረረ (dismissed) ተማሪ የኮርስ ኤግዘምሽን በተመለከተ አዲስ መመሪያ በላከው ደብዳቤ አስታውቃል።

ባለስልጣኑ በሚኒስትሮች ምክርቤት በወጣ ደንብ ቁጥር 515/2014 ዓ.ም በተሰጠው ስልጣን እና ተግባር የትምህርት ጥራትና አግባብነት ለማስጠበቅ እና ለመከታተል ስልጣን ተሰጥቶታል።

በተሰጠው ስልጣንም በመመሪያ 987/2016 ዓ.ም አንቀፅ 13 ንኡስ አንቀፅ 1 መሰረት ማንኛውም ተቋም ስልጣን ባለው አካል የወጣ የቅበላ መስፈርት ያለሟሉ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር እንደማይቻል ደንግጓል፡፡ አንድ ተማሪ በአካዳሚክ ምክንያት ከአንድ ተቋም በሚባረርበት ጊዜ ተማሪው ብቁ አለመሆኑን የሚያሳይ ነው።

በዚህም ተማሪው በአዲስ መልክ ሌላ ተቋም ውስጥ በትምህርት ዘመኑ በተቀመጠው የመቁረጫ ነጥብ ውጤት የሚያስገባው ከሆነ ተመዝግቦ ቢማር ቀድሞ በተባረረበት ተቋም በአንዳንድ ኮርስ ያገኘው ውጤት ኤግዘምት የማይደረግ በመሆኑ ሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተግባራዊ እንዲያደርጉ ማሳስቢያ ተሰጥቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...