የከፋታ የጋዜጠኝነት ስልጠና ተቋም ለ 38ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በትላንትናው ቀን ግንቦት-10-2017 ዓ.ም በኢሊሊ ኢንተርናሽናል ሆቴል አስመርቋል።
“ውበት በልዩነት በጋዜጠኝነት” በሚል መሪ ቃል የምረቃ ስነ-ስርዓታቸውን በ 6 ወር ጊዜ ውስጥ የተማሩትን ትምህርት በተግባር መድረክ ላይ በተለያዩ ፕሮግራሞች ለእንግዶች በማቅረብ አካሂደዋል።
በፕሮግራሙ ላይም አንጋፍ ጋዜጠኞች ተጋባዥ እንግዶች መምህራን እና የተመራቂ ተማሪ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
ተጋባዥ እንግዶች እና መምህራንም ለተመራቂ ተማሪዎች የ አደራ መልዕክት እና ምክር አስተላልፈዋል።
ከፋታ የጋዜጠኝነት ስልጠና ተቋም በ 6 ወር የስልጠና ጊዜ መሠረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና በመስጠት ተማሪዎችን አሰልጥኖ በሙያዉ ብቁ በማድረጉ ረገድ ከፍተኛ የሆነ አስተዋፅኦ እያበረከተ የሚገኝ ተቋም ነው።
