“ዘማይ ጉዞ” የተባለ የሜትር ታክሲ ትራንስፖርት አገልግሎት ጀመረ

Date:

ኩባንያው ስራው የጀመረው በራሱ መኪኖችና አሽከርካሪዎች መሆኑን ተናግሯል።

በዚህም 1,680  የኤሌክትሪክ መኪኖችን ወደ ስራ እንዳሰማራቸው ተነግሯል።

“ዘማይ ጉዞ” ተሳፋሪዎች ንብረታቸውን ረስተው ቢወርዱ ለተሳፋሪው ጥቆማ የሚሰጥ ስርአት የተገጠመለት እንዳለው አስረድቷል።

ተሸከርካሪዎቹ የአደጋ ጊዜ ማሳወቂያ ሳይረን የተገጠመላቸው ስለሆኑ ተሳፋሪ ንብረቱን ጥሎ ቢወርድ እንኳን ሳይረኑ በመጮህ ለተሳፋሪው ጥቆማ ይሰጣል ፥ አሽከርካሪው የተሳፋሪው እቃ ውስጥ እንዳለ ለመንቀሳቀስ ቢሞክር እንኳ መኪናው እንዳይንቀሳቀስ ሲስተሙ ይዘጋበታል ተብሏል፡፡

ዘማይ ጉዞ የራሱ የሆነ  የቻርጅ ጣቢያ፣ ዘመናዊ ጋራዥ እና  መኪና ማጠቢያ አገልግሎቶችን እንዳሟላም ተናግሯል።

ዘማይ ላኪ እና አስመጪ የግል ማህበር ዛሬ ወደ ስራ ካስጀመረው የሜትር ታክሲ የትራንስፖርት አገልግሎት ጎን ለጎን ዘመናዊ የክፍያ ስርዓት ወይም “ዘማይ ብር” የተሰኘ መተግበሪያም ይፋ አድርጓል።

ከጉዞ አገልግሎቱ ጋር ተያይዞ ክፍያዎችን ቀላል እና ፈጣን ለማድረግ ዘማይ ብር  መተግበሪያ ስራ ላይ ውሏል ተብሏል፡፡

ሸገር 102.1

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...