የሆሊውድ “ዎክ ኦፍ ፌም” ኮከብ ያገኘች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊት ዘፋኝ 

Date:

ቤኒናዊቷ አንጀሊክ ኪጆ በሆሊውድ የንግድ ምክር ቤት ተመረጠው በሎስ አንጀለስ ዝነኛው “ዎክ ኦፍ ፌም” ኮከብ ከሚቀበሉ 36 አርቲስቶች አንዷ ሆናለች።

🌟 ከሉፒታ ኒዮንግኦ፣ ቻርሊዝ ቴሮን እና ባሲል ራትቦን ከመሳሰሉ ትውልደ አፍሪካውያን አርቲስቶች በመቀጠል ታሪክ ሠርታለች።

የቤኒን ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ታሎን “በአስገራሚ ጉዞዋና በዚህ ስኬቷ ለሁሉም ምሳሌ ትሆናለች” ሲሉ የአርቲስቷን “አስደናቂ ተሰጥኦ እና ታታሪነት” አድንቀዋል።

🏆 በረጅም የሥራ ዘመኗ ዘፋኟ አምስት የግራሚ ሽልማቶችን እና በ2023 የፖላር ሙዚቃ ሽልማትን አሸንፋለች። በአምስት ቋንቋዎች ማለትም የደቡብ ቤኒኑን ፎን፣ ፈረንሳይኛ፣ ዮሩባ፣ ሚና እና እንግሊዝኛ ትናገራለች።

የ64 ዓመቷ አንጀሊክ ኪጆ የዩኔስኮ የበጎ ፈቃድ አምባሳደር እንዲሁም በአፍሪካ ያሉ ወጣት ሴቶችን የሚያስተምር እና የሚደግፍው የባቶንጋ ፋውንዴሽን መሥራች ናት፡፡ 

“ዎክ ኦፍ ፌም” ከዋክብት የሚደምቁበት ቀን ገና አልተገለጸም፤ ነገር ግን አንድ ነገር እርግጥ ነው፤ ይህም አንጀሊክ ኪጆ ሆሊውድን ማብራቷ ነው!

👉 የሆሊዉድ “ዎክ ኦፍ ፌም” – በሆሊዉድ ኢለቫርድ እና ቫይን ጎዳና ከ2 ሺህ 700 በላይ በቴራዞ እና በነሐስ ኮከቦች ተንቆጥቁጦ የተዘረጋ ታሪካዊ የእገረኞች መንገድ ነው፡፡ የጥብብ ኢንዱስትሪ ሰዎች ላበረከቱት አስተዋፅኦ ክብር የሚሰጥበት ነው፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት በዛሬ ዕትሟ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ነሔሴ 16 2018 ዓ.ም ገበያ...

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...