የመታሰቢያ ጥሪ ለአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ

Date:

በቅርቡ በሞት የተለየን ድንቅ የጥበብ ሰው አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ተወልዶ ባደገበትና የልጅነት ትዝታዎቹ ባሉበት በደብረ ፅጌ ቅዱሥ ዑራኤል ቤተክርስቲያን ታላቅ የመታሰቢያ እና የጸሎት መርሐ-ግብር ተሰናድቷል።

የአካባቢው ወጣቶች በጋራ ባዘጋጁት በዚህ መንፈሳዊ መድረክ ላይ፤ የሻማ ማብራት ስነ-ስርዓት የሚከናወን ሲሆን ብፁሃን አባቶች፣ መምህራነ ወንጌል፣ ዘማሪያን እንዲሁም የስራ ባልደረቦቹና ቤተሰቦቹ ይታደማሉ።

የአርቲስቱ አድናቂዎች፣ የጥበብ ቤተሰቦችና ወዳጆች ሁሉ በዚህ የክብር መርሐ-ግብር ላይ በመገኘት አብራችሁን እንድትሆኑ የዑራኤል አካባቢ ወጣቶች ጥሪያቸውን ያቀርባሉ።

መርሐ-ግብሩ የሚከናወንበት፦

  • ቀን፦ አርብ ጥር 15 ቀን 2018 ዓ.ም
  • ሰዓት፦ ከቀኑ 10:00 ጀምሮ
  • ቦታ፦ ደብረ ፅጌ ቅዱሥ ዑራኤል ቤተክርስቲያን (ዑራኤል)

ለወንድማችን ነፃነት ወርቅነህ የዘላለም እረፍትን እንመኛለን።

ነፍስ ይማር!

ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት መረጃውን ያድርሱ።

Via የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል አካባቢ ወጣቶች መንፈሳዊ የአገልግሎት ማህበር ነን

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...