በቅርቡ በሞት የተለየን ድንቅ የጥበብ ሰው አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ተወልዶ ባደገበትና የልጅነት ትዝታዎቹ ባሉበት በደብረ ፅጌ ቅዱሥ ዑራኤል ቤተክርስቲያን ታላቅ የመታሰቢያ እና የጸሎት መርሐ-ግብር ተሰናድቷል።
የአካባቢው ወጣቶች በጋራ ባዘጋጁት በዚህ መንፈሳዊ መድረክ ላይ፤ የሻማ ማብራት ስነ-ስርዓት የሚከናወን ሲሆን ብፁሃን አባቶች፣ መምህራነ ወንጌል፣ ዘማሪያን እንዲሁም የስራ ባልደረቦቹና ቤተሰቦቹ ይታደማሉ።
የአርቲስቱ አድናቂዎች፣ የጥበብ ቤተሰቦችና ወዳጆች ሁሉ በዚህ የክብር መርሐ-ግብር ላይ በመገኘት አብራችሁን እንድትሆኑ የዑራኤል አካባቢ ወጣቶች ጥሪያቸውን ያቀርባሉ።
መርሐ-ግብሩ የሚከናወንበት፦
- ቀን፦ አርብ ጥር 15 ቀን 2018 ዓ.ም
- ሰዓት፦ ከቀኑ 10:00 ጀምሮ
- ቦታ፦ ደብረ ፅጌ ቅዱሥ ዑራኤል ቤተክርስቲያን (ዑራኤል)
ለወንድማችን ነፃነት ወርቅነህ የዘላለም እረፍትን እንመኛለን።
ነፍስ ይማር!
ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት መረጃውን ያድርሱ።
Via የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል አካባቢ ወጣቶች መንፈሳዊ የአገልግሎት ማህበር ነን
