የመኾኒ ከተማ ነዋሪዎች  በህወሓት ላይ የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ

Date:

በመቶዎች የሚቆጠሩ የደቡብ ትግራይ መኾኒ ከተማ ነዋሪዎች፣ ዛሬ በሕወሓት ላይ የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸውን የክልሉ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ነዋሪዎቹ ሰልፍ የወጡት፣ ሕወሓት የደቡብ ትግራይ አስተዳደራዊ መዋቅሮችን አፍርሶ በድጋሚ ለማደራጀት ማቀዱን የሕወሓት ሊቀመንበር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል በቅርቡ ለወይን መጽሄት በሠጡት ቃለ ምልልስ መናገራቸውን በመቃወም ነው።

በተቃውሞ ሰልፉ ላይ”የራያ ህዝብ ድምፅ ይከበር፣ የደብረፂዮንን መግለጫ አጥብቀን እንቃወማለን፣ በመስዋዕትነት ስም ህዝብ መማገድ ይቁም” የሚሉ መፈክሮች ተስተጋብተዋል፡፡

ከትናንት ወዲያ በደቡብ ትግራይ የማይጨው ከተማ ነዋሪዎች፣ ተመሳሳይ የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸው ይታወሳል።

(ዋዜማ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...