የሩሲያ-ዩክሬን ድርድር አሁናዊ መረጃዎች

Date:

▪️ ዛሬ ጠዋት የዩክሬን ልዑካን ከአሜሪካ እና ቱርክ ተወካዮች ጋር በኢስታንቡል ተወያይተዋል።

▪️የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሃካን ፊዳን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን ቀጥሎ የተደረገው ውይይት ለጋዜጠኞች ዝግ ነበር።

▪️ ድርድሩ ለሁለት ሰዓታት ያህል ቆይቷል።

▪️ከድርድሩ መጠናቀቅ በኋላ የሩሲያ ዋና ተደራዳሪ ቭላድሚር ሜዲንስኪ መግለጫ ሰጥተዋል።

▪️የሩሲያ ልዑካን በድርድሩ ውጤት አጥጋቢ እንደነበር ፣ 1 ሺህ የጦር እስረኞችን ለመለዋወጥ እንደ ተስማሙ እንዲሁም ሞስኮ ንግግሩን ለመቀጠል ዝግጁ መሆኗን ዋና ተደራዳሪው አጽንኦት ሰጥተዋል።

▪️ከድርድሩ በኋላ ዜለንስኪ፣ ማክሮን፣ ሜርዝ፣ ስታርመር እና ቱስክ ከትራምፕ ጋር ተነጋግረዋል።

▪️ ትራምፕ ዛሬ ምሽት የዩክሬንን የሰላም ጉዳይ ለመወያየት ለፑቲን ሊደውሉ እንደሚችሉ አሳዉቀዋል።

▪️የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ እንደገለጹት በፑቲን እና ትራምፕ መካከል የሚደረጉ ግንኙነቶች ሰላምን ለማምጣት እጅግ አስፈላጊ ናቸው።

▪️የሩሲያ እና የዩክሬን ልዑካን ሌላ ዙር ስብሰባ ለማድረግ መሰረታዊ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አስታውቀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...

የብሔር ፌደራሊዝምን ለማስቀጠል “የቆረጡ” ተመካካሪዎች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 14ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች የአጀንዳ...

“የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው” ፓትርያርኩ

የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው...