የሲሚንቶ ፉብሪካዎች በግብዓት አቅርቦት ዙርያ ምክክር ተደረገ

Date:

የሲሚንቶ ፉብሪካዎች ምርታቸውን ማሳደግ በሚችሉበትና በሲሚንቶ ግብዓት አቅርቦት ዙርያ ምክክር መካሄዱን የማዕድን ሚኒስቴር ሚኒስትር ገለጹ፡፡ የማዕድን ሚኒስትሩ ታከለ ኡማ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት በስራ ላይ ያሉ የሲሚንቶ ፉብሪካዎች የሲሚንቶ ምርታቸውን ለማሳደግ በሚያስችሉን ጉዳዮችና የግብአት አቅርቦት ዙሪያ ከሲሚንቶ ፋብሪካ ኃላፊዎች እና የክልል ማዕድን ኃላፊዎች ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡በውይይቱ ላይ በቅርቡ ስራ ለመጀመር አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረገ ያለው የመሶቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ መሳተፉን ጠቅሰዉ ስራውን ለመጀመር የሚያስችሉ የግብአት አቅርቦት እንዲያገኝ መደረጉን ገልጸዋል፡፡ በውይይቱ አዲስ ለሚገነቡ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች መደረግ ስላለበት ድጋፍ መወያየታቸዉንና በተለይ ክልሎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባኦት ቅድስት...

በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም ዓይናቸው በጽኑ መታመሙን ጠበቃቸው ገለጹ

ከሁለት ዓመት በላይ በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም አበራ...

ንግድ ባንክ “ስታርፔይ” የተሰኘ አዲስ መተግበሪያ ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንክ ሥርዓቱን ይበልጥ ዘመናዊና ቀልጣፋ...

በኢትዮጵያ በካንሰር ከሚያዙ ሕፃናት መካከል 75 በመቶ የሚሆኑት ህክምና አያገኙም

በኢትዮጵያ በየዓመቱ በካንሰር ከሚጠቁ ከ6 ሺህ እስከ 8 ሺህ...