የሲሚንቶ ፉብሪካዎች በግብዓት አቅርቦት ዙርያ ምክክር ተደረገ

Date:

የሲሚንቶ ፉብሪካዎች ምርታቸውን ማሳደግ በሚችሉበትና በሲሚንቶ ግብዓት አቅርቦት ዙርያ ምክክር መካሄዱን የማዕድን ሚኒስቴር ሚኒስትር ገለጹ፡፡ የማዕድን ሚኒስትሩ ታከለ ኡማ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት በስራ ላይ ያሉ የሲሚንቶ ፉብሪካዎች የሲሚንቶ ምርታቸውን ለማሳደግ በሚያስችሉን ጉዳዮችና የግብአት አቅርቦት ዙሪያ ከሲሚንቶ ፋብሪካ ኃላፊዎች እና የክልል ማዕድን ኃላፊዎች ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡በውይይቱ ላይ በቅርቡ ስራ ለመጀመር አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረገ ያለው የመሶቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ መሳተፉን ጠቅሰዉ ስራውን ለመጀመር የሚያስችሉ የግብአት አቅርቦት እንዲያገኝ መደረጉን ገልጸዋል፡፡ በውይይቱ አዲስ ለሚገነቡ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች መደረግ ስላለበት ድጋፍ መወያየታቸዉንና በተለይ ክልሎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው” ፓትርያርኩ

የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው...

“ንባብ ለህይወት!” ታላቅ የንባብ ሳምንት እና የመጻሕፍት አውደ ርዕይ

የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት እና የንባብ ለህይወት...

በኢትዮጵያ ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ ጋር ይኖራሉ

በኢትዮጵያ ከ10 ሚልዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ እና ከ2...

የቶዮታ ኮሮላ መኪና በኤሌክትሪክ ሊመጣ ነዉ

የዓለማችን ግዙፍ የመኪና አምራች የሆነው ቶዮታ፤ እንደ ቴስላ እና...