የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

Date:

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ተቋሙ አስታውቋል።

ተርነር እ.ኤ.አ በ1980 የመጀመሪያውን የ24 ሰዓት የኬብል የዜና አውታር በመክፈት በሚዲያው ዘርፍ አብዮት የፈጠሩ ሰው ነበሩ። በተለይም በገልፍ ጦርነት ወቅት በሰሩት የቀጥታ ስርጭት ዘገባ ዓለም አቀፍ ዝናን ያተረፉ ሲሆን፣ የእሳቸው ስኬት እንደ ፎክስ ኒውስ ላሉ ሌሎች ታላላቅ ጣቢያዎች መፈጠር ፈር ቀዳጅ ሆኗል።

የሲኤንኤን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ማርክ ቶምፕሰን ተርነርን “ቁርጠኛና ፍርሃት የማያውቁ መሪ” ሲሉ የገለጿቸው ሲሆን፣ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው፣ ተርነር በታሪክ ውስጥ ትልቅ አሻራ ካሳረፉ ታላላቅ ሰዎች አንዱ መሆናቸውን ገልጸዋል። ተርነር በሚዲያው ዘርፍ ብቻ ሳይሆን በስፖርትና በበጎ አድራጎት ስራዎቻቸውም የሚታወቁ አንጋፋ ስብዕና ነበሩ።

በተለይም ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የ1 ቢሊዮን ዶላር እርዳታ በማድረግ የሚታወሱት ቴድ ተርነር፣ በ938 በኦሃዮ ተወልደው የአምስት ልጆች አባት ለመሆን በቅተዋል።

እኒህ ታላቅ ሰው በሚዲያው ዓለም ላይ ጥለውት ያለፉት አሻራ ለትውልድ ሲዘከር የሚኖር የታሪክ አካል ሆኖ ይቀጥላል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል

ኢትዮጵያ  በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ  በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ...