የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አ.ማ በሱፐር ስፖርት የቀጥታ ስርጭት ሽፋን የማያገኙ የ2017 ዓ.ም የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎችን ለትርፍ በማይውል መንገድ በማህበራዊ ትስስር ገፁ (በፌስቡክ) በቀጥታ ስርጭት እንደሚያስተላልፍ ይታወቃል።
የ23ኛ ሳምንት ጨዋታ በሚተላለፍበት ወቅት የደጋፊዎች ያልተገቡ የእርስ በእርስ ስድቦች በፌስቡክ ኮሚኒቲ ስታንዳርድ (bullying and harassment, hate speech) ምክንያት ገፁ ለሦስት ቀናት ከቀጥታ ስርጭት ስለታገደ የ24ኛ ሳምንት የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ቀን ጨዋታዎች በአክሲዮን ማኅበሩ የፌስቡክ ገፅ አይተላለፉም።
ነገር ግን ሁሉም ጨዋታዎች የሚቀረፁ በመሆኑ የጨዋታው እንቅስቃሴ ሃይላይት ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ እንዲሁም ግቦች ጨዋታው እየተከናወነ የቪድዮ ምስሎቹ የሚለቀቁ ይሆናል።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አ.ማ
