የቃሊቲ ወደብና ተርሚናል ግንባታ በ510 ሚሊየን ብር ሊካሄድ ነው

Date:

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ከ510 ሚሊየን ብር በሚልቅ ወጪ የቃሊቲ ወደብና ተርሚናልን ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ለመገንባት የሚያስችል ስምምነት ከኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ጋር ተፈራርሟል።

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ በሪሶ አመሎ (ዶ/ር) እንደተናገሩት የቃሊቲ ወደብና ተርሚናል ለአገልግሎት ሰጪዎችም ሆነ ለተጠቃሚዎች ምቹ አይደለም። በመሆኑም በስምምነቱ መሰረት ፕሮጀክቱ በወቅቱ እንዲጠናቀቅና ምቹ የስራ አካባቢ ለመፍጠር እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

የቃሊቲ ወደብና ተርሚናልን የግቢ ውስጥ መንገድ እና የኮንቴይነር ተርሚናል ለማሻሻል ከ510 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት የተመደበ ሲሆን፣ ግንባታው በስድስት ወራት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...