የቃሊቲ ወደብና ተርሚናል ግንባታ በ510 ሚሊየን ብር ሊካሄድ ነው

Date:

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ከ510 ሚሊየን ብር በሚልቅ ወጪ የቃሊቲ ወደብና ተርሚናልን ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ለመገንባት የሚያስችል ስምምነት ከኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ጋር ተፈራርሟል።

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ በሪሶ አመሎ (ዶ/ር) እንደተናገሩት የቃሊቲ ወደብና ተርሚናል ለአገልግሎት ሰጪዎችም ሆነ ለተጠቃሚዎች ምቹ አይደለም። በመሆኑም በስምምነቱ መሰረት ፕሮጀክቱ በወቅቱ እንዲጠናቀቅና ምቹ የስራ አካባቢ ለመፍጠር እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

የቃሊቲ ወደብና ተርሚናልን የግቢ ውስጥ መንገድ እና የኮንቴይነር ተርሚናል ለማሻሻል ከ510 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት የተመደበ ሲሆን፣ ግንባታው በስድስት ወራት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!! በክርስቲያኖች ዘንድ ጥምቀት...

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባኦት ቅድስት...

በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም ዓይናቸው በጽኑ መታመሙን ጠበቃቸው ገለጹ

ከሁለት ዓመት በላይ በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም አበራ...

ንግድ ባንክ “ስታርፔይ” የተሰኘ አዲስ መተግበሪያ ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንክ ሥርዓቱን ይበልጥ ዘመናዊና ቀልጣፋ...