የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ከ510 ሚሊየን ብር በሚልቅ ወጪ የቃሊቲ ወደብና ተርሚናልን ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ለመገንባት የሚያስችል ስምምነት ከኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ጋር ተፈራርሟል።
የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ በሪሶ አመሎ (ዶ/ር) እንደተናገሩት የቃሊቲ ወደብና ተርሚናል ለአገልግሎት ሰጪዎችም ሆነ ለተጠቃሚዎች ምቹ አይደለም። በመሆኑም በስምምነቱ መሰረት ፕሮጀክቱ በወቅቱ እንዲጠናቀቅና ምቹ የስራ አካባቢ ለመፍጠር እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
የቃሊቲ ወደብና ተርሚናልን የግቢ ውስጥ መንገድ እና የኮንቴይነር ተርሚናል ለማሻሻል ከ510 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት የተመደበ ሲሆን፣ ግንባታው በስድስት ወራት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሏል።
