የቤንዚል፣ የነጭ ናፍጣ እና የኬሮሲን ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል

Date:

የነሐሴ ወር የቤንዚል፣ የነጭ ናፍጣ፣ የኬሮሲን እና የአውሮፕላን ነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል አለ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፡፡

ሚኒስቴሩ ከዛሬ ምሽት 12 ሰዓት ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ የነሐሴ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ማስተካከያ ይፋ አድርጓል፡፡

በዚህም መሰረት የቤንዚል፣ የነጭ ናፍጣ፣ የኬሮሲንና የአውሮፕላን ነዳጅ ምርቶች የመሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ብሏል፡፡

በሌላ በኩል ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 127 ነጥብ 22 ብር እንዲሁም ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 124 ነጥብ 55 ብር ብቻ እንዲሸጥ መወሰኑን የሚኒስቴሩ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር ወንድሙ ፍላቴ  ተናግረዋል፡፡

የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎችም በነዳጅ ውጤቶች ግብይት በአዋጁና በአሠራር መመሪያው መሠረት ውሳኔውን ተግባራዊ እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አርሰናል ከቦርንማውዝ በጉጉት የሚጠበቅ ጨዋታ

በ32ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ቀን...

በአሜሪካ እና ኢራን ድርድር ላይ የሚነሱ አራት ቁልፍ ጥያቄ

በፓኪስታን የሚደረገው የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር እየተጠበበፓኪስታን ነገር ግን...

መንገዳችን ረጅም፣ ጉዟችን ፈታኝ መሆኑን እናውቃለን

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል...

የተመድ ዋና ጸሐፊ ኢራን እና አሜሪካ “በቅን ልቦና” ወደ ድርድሩ እንዲገቡ ጠየቁ

የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አሜሪካ እና ኢራን...