የሀዋሳ የቀድሞው ከንቲባ ስለታቸውን አስገቡ ምስክርነትም ሰጡ

Date:

“ቅዱስ ገብርኤል ሆይ አውጣኝ አልኩት ጸሎቴን ሰምቶ አወጣኝ”……”የቀድሞው የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ምስክርነት !!!

የሐዋሳ ከተማ የቀድሞ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ጸጋዬ ቱኬ በሐሰት በተከሰሱበት የክስ መዝገብ 13 ዓመት ተፈርዶባቸው ወደ ወህኒ ሲወረወሩ በእስር ቤት ሆነው ለቅዱስ ገብርኤል ጸሎት ልመናንን አቀረቡ።

“በአዉደ ምህረትህ ቆሜ ስለክብርህ መስከርያለሁና ለቂርቆስና እየሉጣ የደረስክ ቅዱስ ገብርኤል ሆይ አንተ ድረስልኝ ! የኔ እዉነት ተቀብሮ እንዳይቀር እርዳኝ” ሲል ተለማመኑት።

እነሆ መላእከ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል በግፍ እና በበደል ለተገፉት ፈጥኖ መድረስ ባህሪው ነው እና ሰኔ 12 የዓመቱ ሚካኤል ቀን የባህራንን የሞት ደብዳቤ የሻረ አምላክ ከተፈረደባቸው የ 13 ዓመት የሐሰት እስራት ፍርድ በይግባኝ ነጻ ተብለው በሠላም ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተቀላቀሉ።

እነሆ ድንቅ ታምር ያደረገላቸው እና ጸሎት ልመናቸውን የሰማውን ቅዱስ ገብርኤል በአውደ ምህረት ቆመው ትላንት አመስግነዋል። ስለታቸውንም 5000 ብር አስገብተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...