የተመጣጠነ የምግብ ችግርን ለመቅረፍ አስገዳጅ መመሪያ ተዘጋጀ

Date:

የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በንጥረ ነገሮች የበለፀጉ የዘይትና ዱቄት ምርቶችን ለመመዝገብ የሚያስችል አስገዳጅ መመሪያ ማዘጋጀቱን ተከትሎ በመመሪያው ላይ አስተያየት እንዲሰጡበት በሐዋሳ ቅርንጫፍ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በተዘጋጀው መድረክ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቅርንጫፉ የምግብ ተቋማት ህግ ማስፈፃምና ኢንስፔክሽን ዴስክ ኃላፊ አቶ ብሩህ አለማየሁ እንደተናገሩት የተመጣጠነ የምግብ እጥረተ የህብረተሰብ ጤና ችግር መሆኑን ገልፀው መንግስት የህዝብን የአመጋገብ ስርዓት ለማሻሻል የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡

እንደአቶ ብሩህ ንግግር ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን መሰረት ምግቦችን በማዕድን፣ ቫይታሚን እና ሌሎች ንጥረ ነገሮች ለማበልፀግ አስገዳጅ መመሪያ ማዘጋጀቱንና ይህ መድረክም ባለድርሻ አካላት በዋነኝነት የዘይትና የዱቄት አምራቾች አስተያየት እንዲሠጡበት የተዘጋጀ ነው ብለዋል፡፡

በመድረኩ በምግብ ማበልፀግ አስፈላጊነት እና የዱቄትና የዘይት አምራች ተቋማት ሊዘረጉት ስለሚገባው የዉስጥ ጥራት ዝርጋታ ፅሁፎች የቀረቡ ሲሆን ባለስልጣኑ ያዘጋጀው አስገዳጅ የምግብ ማበልፀግ መመሪያ ለውይይት ቀርቦ ሠፊ ውይይት ተደርጓል፡፡

በውይይቱ በሐዋሳ ቅርንጫፍ ዱቄትና ዘይት ማምረቻ ፈቃድ ወስደው እየሰሩ ያሉ ተቋማት የተሳተፉ ሲሆን ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችም የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ሐዋሳ ቅርንጫፍና ከዋናው ቢሮ በተገኙ ባለሙያዎች ማብራሪያ ሲሰጥ የቅርንጫፉ  ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ንማኔ እንደተናገሩት የምግብ ማበልፀጉን ተግባራዊ የማያደርጉ ተቋማት ላይ እርምጃ መውሰዱ ይቀጥላል ብለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...