ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ጋር ተወያዩ

Date:


የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዬሶን አርካዲዮ ሜኔስ ኮፕቴን በጽ/ ቤታቸው በመቀበል ውይይት አድርገዋል።

በውይይታቸውም ሁለቱ አገራት በትምህርቱ ዘርፍ በትብብር መስራት የሚችሉባቸውን ጉዳዮች አንስተው ተወያይተዋል።

በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የኮሎምቢያ አምባሳደር በጽ/ቤታቸው ተቀብለው በማነጋገራቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸው በትምህርቱ ዘርፍ በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ ጉዳዮችን ለአምባሳደሩ አንስተውላቸዋል።

በተለይም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ በተማሪዎች ነጻ የትምህርት እድል፣ በሙዚቃና ባህል ልውውጥ እንዲሁም በሌሎች ጉዳዮች በትብብር መስራት እንደሚቻልም አብራርተዋል።

በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዬሶን አርካዲዮ ሜኔስ ኮፕቴ በበኩላቸው ኮሎምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ኤምባሲዋን በአዲስ አበባ መክፈቷን ገልጸው በትምህርቱ ዘርፍም ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር መስራት እንደምትፈልግ ተናግረዋል።

አክለውም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ነጻ የትምህርት እድልና የባለሙያ ልውውጥ፣ በከፍተኛ ትምህርት የሰላም ግንባታ እንዲሁም በሙዚቃና ባህል ልምድ ልውውጥ በማድረግ ረገድ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉም አንስተዋል።

ሁለቱ አካላት በቀጣይ በሚኖራቸው ግንኙነቶች በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ የጋራ ትብብሮችን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚያደርጉት ድርድር እስኪጠናቀቅ ድረስ የተኩስ አቁሙ መራዘሙን አስታወቁ

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፓኪስታን ጥያቄ መሠረት ከኢራን ጋር የገቡትንየተኩስ...

ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የሚውል የ40 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ተፈቀደ

የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የልማት ክንፍ የሆነው ኢአይቢ ግሎባል (EIB...

ሃይንከን በአልኮል መጠኑ ጠንከር ያለ ቢራ ለኢትዮጵያ ገበያ አስተዋወቀ

ሃይንከን ኢትዮጵያ በእለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ የሆነውን ዴሰፔራዶስ (Desperados)...