የትራምፕ አስተዳደር የጉዞ እገዳ ሊጥልባቸው ነው የተባሉ 41 ሀገራት ውስጥ ኢትዮጵያ ?

Date:

የትራምፕ አስተዳደር በደርዘን የሚቆጠሩ ሀገራት ዜጎች ላይ የጉዞ ገደቦችን ለማውጣት ዝርዝር ማዘጋጀቱን ሮይተርስ አገኘሁት ያለውን ሰነድ ጠቅሶ ዘግቧል ።

በስደተኛ ላይ ጠንካራ ፖሊሲ የሚያራምዱት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ወደ ሀገራቸው እየመለሷቸው ከሚገኙ ህገ ወጥ ስደተኞች ባለፈ በተለያዩ ሀገራት ዜጎች ላይ የጉዞ ክልከላ አውጥተዋል፡፡

ክልከላ የተላለፈባቸው ሀገራት ዜጎች ለስራ ፣ ለጉብኝት ፣ ጥገኝነት በመጠየቅ እና በተለያዩ የአሜሪካ ቪዛዎች ወደ አሜሪካ ምድር መግባት አይችሉም፡፡

ሮይተርስ ተመለከትኩት ያለው የጉዞ ክልከላ ሰነድ በድምሩ 41 አገሮችን በሶስት የተለያዩ ቡድኖች ይዘረዝራል።

 የመጀመሪያው አፍጋኒስታን ፣ ኢራን ፣ ሶሪያ ፣ ኩባ እና ሰሜን ኮሪያ እና ሌሎችንም ጨምሮ በ10 ሀገራት ላይ ሙሉ የቪዛ እገዳ ጥሏል፡፡

በሁለተኛው ረድፍ ኤርትራ፣ ሄይቲ፣ ላኦስ፣ ምያንማር እና ደቡብ ሱዳን ከፊል እገዳዎች የተጣሉባቸው ሲሆን ይህም በቱሪስት ፣ በተማሪ እንዲሁም ሌሎች የስደተኛ ቪዛዎች ላይ ተፅዕኖ ይኖረዋል ነው የተባለው።

በሶስተኛው ቡድን ውስጥ ቤላሩስ፣ ፓኪስታን እና ቱርክሜኒስታንን ጨምሮ በአጠቃላይ 26 ሀገራት መንግስታቸው በ60 ቀናት ውስጥ በኢሜግሬሽን አገልግሎት ላይ የሚታዩ ጉድለቶችን ለመፍታት ጥረት ካላደረገ የከፊል የጉዞ እገዳ እንደሚጣልባቸው ሰነዱ አመላክቷል፡፡

አንድ ስማቸው ያለተገለጸ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባልደረባ ለሮይተርስ እንደተናገሩት በዝርዝሩ ላይ ለውጦች ሊኖሩ እንደሚችሉ እና የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮን ጨምሮ አስተዳደሩ የጉዞ ክልከላ ሰነዱን አላጸደቀውም፡፡

ያሁኑ የጉዞ ክልከላ ትራምፕ በመጀመሪያ የስልጣን ጊዜያቸው በ2018 በርካታ ሙስሊሞች በሚገኙባቸው 7 ሀገራት ላይ ካወጡት የጉዞ ክልከላ ጋር የሚመሳሰል ነው፡፡

ይህ የትራምፕ የጉዞ እገዳ በ2018 በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ከመጽደቁ በፊት ለረጅም ጊዜ ተይዞ እንደነበር ይታወሳል፡፡

 ትራምፕ በጥር 20 ከፈረሟቸው የስራ አስፈጻሚ ትዕዛዞች መካከል ወደ አሜሪካ የሚገባ ማንኛውም የውጭ ሀገር ዜጋ ለብሔራዊ ደህንነት ስጋት አለመሆኑን ለማረጋገጥ የተጠናከረ ማጣራት እንዲደረግበት የሚጠይቀው መመሪያ ይጠቀሳል፡፡

በዚህ መመሪያ ላይ በመረጃዎቻቸው ጉድለት እና በተለያዩ ምክንያቶች በከፊል እና ሙሉ ለሙሉ ወደ አሜሪካ ከመግባት መታገድ የሚገባቸውን ሀገራት ዝርዝር ካቢኔው እስከ መጋቢት 21 እንዲያቀርብ ያዛል፡፡

( የሀገራቱን ዝርዝር ከምስሉ ይመልከቱ )

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን የመከላከያ ስምምነቶችና የፖለቲካዊ ድጋፎች

በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን የጸጥታ ስጋት ተከትሎ፣ ጣሊያን ለባህረ...

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ”ንዋይ” የተሰኘ መተግበሪያን ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ዜጎች...

የነዳጅ እጥረት አሽከርካሪዎችን ለከፋ እንግልት እየዳረገ ነው

በአዲስ አበባ እና በልዩ ልዩ የክልል ከተሞች የሚስተዋለው የነዳጅ...

ሼክ ኢብራሂም ቱፋ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት ሀዘናቸውን ገለጹ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼክ ኢብራሂም...