የትራንስፖርት ክልከላዉ ተነስቷል

Date:



‎በጂንካ በተከሰተዉ የማርበርግ ቫይረስ ስርጭት ምክንያት ተጥሎ የነበረዉ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ክልከላ መነሳቱን የአሪ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ኃላፊ አቶ ደምበላሽ አቦነሀሰ  ተናግረዋል።

‎ለክልከላዉ መነሳት ምክንያት የሆነዉ አሁናዊዉ የማርበርግ ቫይረስ ስርጭት መቀነስና በትራንስፖርት መቋረጥ ምክንያት ማህበረሰቡ የእለት ተዕለት እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ መምጣቱን የዞኑ ግብረሃይል ከገመገመ በኋላ መሆኑን ገልፀዋል።

‎በመሆኑ ከቀን 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ ክልከላው እንዲነሳ መወሰኑን  የገለፁት ኃላፊዉ ጉዞዎች ግን ከወትሮዉ በተለየ በጥንቃቄ መሆን እንዳለባቸውና በየመናኻሪያ የሚደረጉ የግንዛቤ ማስጨበጫና የጥንቃቄ ሂደቶች ተጠናክረዉ እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

‎ሕብረተሰቡና የተሽከርካሪ ባለንብረቶችም ይህንኑ በመረዳት አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉም አቶ ደምበላሽ አሳስበዋል።

@tikvahethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...