የቶዮታ ኮሮላ መኪና በኤሌክትሪክ ሊመጣ ነዉ

Date:

የዓለማችን ግዙፍ የመኪና አምራች የሆነው ቶዮታ፤ እንደ ቴስላ እና የቻይናው BYD ያሉ የኤሌክትሪክ መኪና አምራቾች የገበያውን አሰራር በፍጥነት እየቀየሩት መሆኑን አስታውቋል።

ኩባንያው ባለፉት 60 ዓመታት ከ57 ሚሊዮን በላይ በመሸጥ በዓለም ቀዳሚ የሆነችውን «ኮሮላ» መኪና አዲስ ሞዴል ላይ ትልቅ ትኩረት አድርጓል።

የኩባንያው ሊቀመንበር አኪዮ ቶዮዳ፣ በድሮ ስኬት መታበይ አደጋ መሆኑን በመጥቀስ፣ «በዚህ ከቀጠልን ሁሉም ነገር ያበቃል» ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

የኩባንያው መሐንዲሶችም የቻይና ኩባንያዎች በቴክኖሎጂ እየቀደሟቸው መሆኑን አምነዋል። አዲሱ የኮሮላ መኪና በነዳጅ፣ በሀይብሪድ እና ለመጀመሪያ ጊዜ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሪክ የሚሰራ አማራጭ ይዞ ይወጣል።

ቶዮታ መኪናው ገበያ ላይ የሚወጣበትን ቀን እስካሁን ይፋ ባያደርግም፣ ይህ አዲሱ የኮሮላ ፕሮጀክት ለኩባንያው የወደፊት ዕጣ ፈንታ እጅግ ወሳኝ ሥራው መሆኑን ገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...