የቻይና ኩባንያ በኢትዮጵያ የአየር ታክሲና ሰው አልባ ተሽከርካሪዎችን ሊያመርት ነው

Date:

የቻይናው ሻንሀይ ላውንች ዲዛይን አውቶሞቲቭ ኩባንያ በኢትዮጵያ ውስጥ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ የአየር ታክሲና ሰው አልባ ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን ለማምረት ፍላጎት እንዳለው አስታወቀ።

ይህንንም ፍላጎት ይፋ ያደረገው የኩባንያው ስራ አስኪያጅ ው ሻውሀን ከትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ ነው።

በውይይቱ ወቅት ሚኒስትሩ መንግስት አረንጓዴ ትራንስፖርትን ለማስፋፋት ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸው ጠንካራ የመንግስት ድጋፍ እና የታክስ ማበረታቻዎች ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታዎች መሆናቸውን አስረድተዋል።

የሻንሀይ ላውንች ዲዛይን አውቶሞቲቭ ስራ አስኪያጅ እንዳሉት ኩባንያቸው በኢትዮጵያ ውስጥ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በማምረት ላይ መሰማራት እንደሚፈልግ ገልጸዋል።

ኩባንያው በኤሌክትሪክ የሚሰሩ የአየር ታክሲና ሰው አልባ ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ አውቶሞቢሎችን፣ አውቶብሶችንና የጭነት ተሽከርካሪዎችን እንደሚያመርትም አብራርተዋል።

ቅዳሜገበያ

Ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...