የቻይና ኩባንያ በኢትዮጵያ የአየር ታክሲና ሰው አልባ ተሽከርካሪዎችን ሊያመርት ነው

Date:

የቻይናው ሻንሀይ ላውንች ዲዛይን አውቶሞቲቭ ኩባንያ በኢትዮጵያ ውስጥ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ የአየር ታክሲና ሰው አልባ ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን ለማምረት ፍላጎት እንዳለው አስታወቀ።

ይህንንም ፍላጎት ይፋ ያደረገው የኩባንያው ስራ አስኪያጅ ው ሻውሀን ከትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ ነው።

በውይይቱ ወቅት ሚኒስትሩ መንግስት አረንጓዴ ትራንስፖርትን ለማስፋፋት ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸው ጠንካራ የመንግስት ድጋፍ እና የታክስ ማበረታቻዎች ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታዎች መሆናቸውን አስረድተዋል።

የሻንሀይ ላውንች ዲዛይን አውቶሞቲቭ ስራ አስኪያጅ እንዳሉት ኩባንያቸው በኢትዮጵያ ውስጥ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በማምረት ላይ መሰማራት እንደሚፈልግ ገልጸዋል።

ኩባንያው በኤሌክትሪክ የሚሰሩ የአየር ታክሲና ሰው አልባ ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ አውቶሞቢሎችን፣ አውቶብሶችንና የጭነት ተሽከርካሪዎችን እንደሚያመርትም አብራርተዋል።

ቅዳሜገበያ

Ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ...

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...