የኢትዮጵያ ደረጃዎች ቦርድ አዲስ ምልክት አጸደቀ

Date:

የኢትዮጵያ ደረጃዎች ቦርድ መጋቢት 23 ቀን 2017 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ወደ ሀገር ውስጥ ለሚገቡ ምርቶች የሚሆን አዲስ የደረጃ ምልክት አጽድቋል።

ይህ ምልክት ከዉጪ የሚገቡና የኢትዮጵያ ደረጃ የወጣላቸውን ምርቶች ከሀገር ውስጥ ምርቶች ለመለየት ያስችላል ተብሏል።

በገበያ ላይ ፍትሃዊ የሆነ ውድድር እንዲኖር እንደሚያደርግ እና ሸማቾች የውጭ ምርቶች ጥራታቸውን ጠብቀው መምጣታቸውን እንዲያውቁ እንደሚረዳ ተገልጿል።

ካፒታል ያገኘዉ መረጃ እንደሚያመለክተዉ ይህ አዲስ የደረጃ ምልክት የኢትዮጵያ ደረጃ ለወጣላቸው ከውጭ ለሚገቡ ምርቶች ብቻ የሚውል ይሆናል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...