የኢትዮጵያ ደረጃዎች ቦርድ መጋቢት 23 ቀን 2017 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ወደ ሀገር ውስጥ ለሚገቡ ምርቶች የሚሆን አዲስ የደረጃ ምልክት አጽድቋል።
ይህ ምልክት ከዉጪ የሚገቡና የኢትዮጵያ ደረጃ የወጣላቸውን ምርቶች ከሀገር ውስጥ ምርቶች ለመለየት ያስችላል ተብሏል።
በገበያ ላይ ፍትሃዊ የሆነ ውድድር እንዲኖር እንደሚያደርግ እና ሸማቾች የውጭ ምርቶች ጥራታቸውን ጠብቀው መምጣታቸውን እንዲያውቁ እንደሚረዳ ተገልጿል።
ካፒታል ያገኘዉ መረጃ እንደሚያመለክተዉ ይህ አዲስ የደረጃ ምልክት የኢትዮጵያ ደረጃ ለወጣላቸው ከውጭ ለሚገቡ ምርቶች ብቻ የሚውል ይሆናል።
