የኃይል ሥርቆት የፈጸሙ 111 ደንበኞች ላይ ክስ ተመሠረተ

Date:



የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሸገር ሪጅን በ8 ወራት ውስጥ አንድ መቶ አስራ አንድ ደንበኞች የኃይል ሥርቆት መፈጸማቸውን ባደረገው ድንገተኛ ምርመራ እና ክትትል ማግኘቱን አስታውቋል።

ሪጅኑ በ196 ሺሕ ደንበኞች ላይ ባደረገው ድንገተኛ ክትትል 13 በስማርት ቆጣሪዎች፣ 69 በቅድመ ነጠላና ባለሦስት ፌዝ ቆጣሪዎች እና በ29 የድህረ-ክፍያ ቆጣሪዎች ላይ ስርቆቱ መፈፀሙን  የሸገር ሪጅን ኢነርጂ ማኔጅመንት ማናጀር አቶ ግርማ ተናግረዋል።

ዘመናዊ ቆጣሪዎች (ስማርት ) ላይ የተደረገው ስርቆት የታወቀው ቆጣሪዎቹ ወደ መረጃ ቋት በሚልኩት መረጃ ነው።የኃይል ስርቆት በፈፀሙ ደንበኞች ላይ ከ 31 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ እንዲከፍሉ በማድረግ ሊባክን የነበረ ከ17 ሚሊየን በላይ ኪዋት ሰዓት ከብክነት ታድገናል ሲሉ ማናጀሩ ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም የኃይል ስርቆት ሲፈጽሙ በተገኙ  ደንበኞች ላይ ክስ መመስረቱ ተገልጿል።የኃይል ስርቆት ተግባር ሲፈፅም የተገኘ አካል በሕግ ከመጠየቁም ባለፈ፣ ይጠቀምበት የነበረው አገልግሎት እንደሚቋረጥ፣ ያለአግባብ ለተጠቀመው የፍጆታ ሂሳብ በታሪፉ መሰረት ተሰልቶ ከዳግም ማስቀጠያ ክፍያና ከተጨማሪ ቅጣት ጋር እንዲከፈል  ይደረጋል፡፡

በተጨማሪም የኃይል ስርቆት መፈፀም በወንጀል የሚያስከስ እና እስከ አምስት ዓመት በእስራት የሚያስቀጣ እንዲሁም እስከ 20 ሺሕ ብር የገንዘብ ቅጣት የሚያስቀጣ ነው ሲሉ አቶ ግርማ ወግበላ ጨምረው መናገራቸውን ብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ዘግቧል።
@ዳጉ_ጆርናል

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...