የአሜሪካ ኤምባሲ አቶ ማሞ ምህረቱን በይፋ አመሰገነ

Date:

በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ፣ ከሰሞኑ ከኃላፊነታቸው በፈቃዳቸው የለቀቁትን የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ በይፋ አመሰገነ፡፡

ኤምባሲው በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈረው መልዕክት፤ አቶ ማሞ ለሰጡት አገልግሎትና ለራዕያቸው  ምስጋና አቅርቧል፡፡

“የአቶ ማሞ ድፍረት የተመላበት አመራር፣ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚና ህዝቧን ወደ ኋላ ይጎትቱ የነበሩ የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባቶችን ለማረም ረድቷል” ብሏል፤ ኤምባሲው።

ኢትዮጵያ እሳቸው መንገድ የጠረጉለትን የኢኮኖሚ ማሻሻያ  እንድትቀጥልም  አሳስቧል።

ኤምባሲው አክሎም፤ “በተለይ ከባድ ተግዳሮቶች  ባሉበት ሁኔታ ውስጥ ለውጥ በጭራሽ ቀላል አይደለም” ሲልም ለሪፎርሙ ዕውቅና በመስጠት የቀድሞውን የብሔራዊ ባንክ ገዢ አመስግኗል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...